Showing posts with label Tewahedo. Show all posts
Showing posts with label Tewahedo. Show all posts

Wednesday, December 10, 2025

St. Raguel to Prophet Elijah (Elias): "Rejoice, For The Time Has Come For You to Ascend to Heaven”

https://rumble.com/v72u8io-st.-raguel-to-prophet-elijah-eliasrejoice-for-the-time-has-come-for-you-to-.html

https://www.bitchute.com/video/zpZ0pSXPYmiC/

😇 አንድ ቀን ነብዩ ኤልያስ ጸሎት እያደረገ ሳለ መልአኩ ቅዱስ ራጉኤል ተገልጾ፡-

"ኃላፊ፣ ጠፊ የኾኑ ሕሊናትን ያሸነፍህ፤ ሞትንም ድል ያደረግህ ተጋዳይ ሆይ ፈጽሞ ደስ ይበልህ፡፡ ወደ ሰማይ የምታርግበት ዘመን ደርሷልና፡፡ ፍጹም ደስታ፣ ፈገግታ፣ ተድላ ከሰፈነበት አገር ትኖራለህ፡፡ ደዌ፣ በሽታ፣ ሞት፣ ኀዘን ከሌለበት፤ በረከት፣ ከሞላበት ቤትም ትገባለህ፡፡ በዚያም የልዑል እግዚአብሔርን ትእዛዝ የሚጽፍ እንደ አንተ ያለ ሄኖክ አለ፡፡ አሁንም ተነሥና ዮርዳኖስን ተሻግረህ ሒድ" አለው፡፡

ደመና ደመና ….. በሠረገላ፤

ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤

በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤…

ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤

ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤

በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤

በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤

አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡

እንኳን ለ ለታላቁ ነብይ ለቅዱስ ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል (የልደት ቀን)አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት ከነብዩ ኤልያስ፣ ነብዩ ሔኖክ፣ ከፓትርያርክ አባታችን ቅዱስ ሔኖክ፣ ከቅዱስ ራጉኤልና ቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በተያያዘ ተዓምር ልላቸው የምችላቸውን አስገራሚ ክስተቶች እየታዘብኩ ነው። በዚህች ምድራችን ላይ ብቻ ሳይሆን በተለይ ፀሐይ ላይ የሆነ ዓለምን ሊለውጥ የሚችል ክስተት በእነዚህ ቀናት እየታዘብን ነው። ከእነ ነብያቱ ሔኖክ እና ኤልያስ መምጣት ጋር የሚገናኝ ክስተት ይሆን? የሆነ ትልቅ ነገር ይሰማኛል!

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነብያት ዝናም በማቆም ብቸኛ ነብይ ቅዱስ ኤልያስ በዘመነ ነገሥታት ከነበሩ ነቢያት አንዱ ነው፤ አባቱ ኢያሴንዩ እናቱ ደግሞ ቶና ይባላሉ፤ አባትና እናቱ በምግባር አሳደጉት፤ ከዚያም ወደ ገዳም ሄደ በጾምና በጾሎት በብሕትውና (በገዳም) ኖረ፤ እርሱ በነበረበት ዘመን ንጉሥ አክአብና ሚስቱ ኤልዛቤል የተባሉ ነበሩ፤ እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን የማያምኑ በጣዖት የሚያመልኩ ነበሩ፤ ድሮ በኢሎፍላውያን እጅ የነበሩት ጣዖታት (ዳጐንና ቤል) በዚያ ዘመን ወደ እስራኤል ገብተው ነበር። ነብዩ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን የሚያውቅና እግዚአብሔርን የሚያመልክ ሰው ነበር። በዚያ ወራትም እግዚአብሔር ለነብይነት ጠራው። እርሱም “እሺ” ብሎ ታዝዞ የእግዚአብሔርን የጸጋ ጥሪ ተቀበለ። ነብዩ ኤልያስ ብዙ ጊዜ ለጉዳይ ካልሆነ ከሰው ጋር መዋል ማደርን አይወድምና መኖሪያውን በተራሮችና በዱር አደረገ፤ በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ ለእርሱ ቤቱ ነበር። (ድርሳን ነብዩ ኤልያስ የታኅሣሥ ወር)

ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ሕዝቡን እግዚአብሔር ከክፉ ነገር እየጠበቀ፣ የእርሱን ስጦታ እየተመገበ ይኖር ነበር፤ እነርሱ ግን ለቤል (ለበዓል) ለተባለ ጣዖት የሚሰግዱ ነበሩ። ይህን ጊዜ ግን ነብዩ ኤልያስ ወደ አክአብ ዘንድ ሄዶ ጣዖት ማምለክ እንደ ሌለበት ሳይፈራ ገሠጸው፤ (ተቆጣው) ጣዖት የሚያመልክ ከሆነ የሚመጣውን መከራ እንዲህ በማለት ነገረው፦ ‹‹በፊቱ የቆምኩት እስራኤል አምላክ ሕያው እግዚአብሔርን ከአፌ ቃል በቀር በእነዚህ ዓመታት ጠልና ዝናም አይሆንም፤ (፩ኛመጽሐፈ ነገሥት ፲፯፥፩) ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር ዝናም ከሰማይ እንዳይወርድ ተከለከለ። ሕዝቡ በኃጢአቱና ጣዖት በማምለኩ ምክንያት ዝናም ስላልዘነበ እህል በማጣት ተጐዳ። ነብዩ ኤልያስን ግን አምላካችን በዋሻ ተቀምጦ ቁራ የሚበላውን እያመጣለት ይመግበው፣ ምንጭ ፈልቆለት ይጠጣ ነበር።

ከዚያም እግዚአብሔር ሕዝቡ በረኀብ እንደተጎዳ ይመለከት ዘንድ ለነብዩ ኤልያስ ምግብ ይወስድለት የነበረውን ቁራ አስቀረበት፤ ነብዩ ኤልያስም ምግብ ፍለጋ ሰራፕታ ወደ ተባለ ሥፍራ ሄደ፤ በዚያም ነብዩ ባሏ የሞተባትና ዮናስ የተባለ ልጅ የነበራትን ሴት አገኘ፤ እርሷም እንጐቻ ጋግራ ብታበላው ቤቷን በበረከት ሞላው። ታዲያ አንድ ቀን ልጇ ታሞ ሞተባት፤ ነብዩ ኤልያስም በጸሎቱ የሞተውን ልጇን (ሕፃኑ ዮናስን) ከሞትም በጸሎቱ አስነሳላት። (፩ኛነገሥት ፲፯፥፲፯)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ነብዩ ኤልያስ “ለምን ጣዖት ታመልካላችሁ” በማለት ዝናም እንዳይዘንብ ቢያደርግም እግዚአብሔር ለሕዝቡ አዘነ፤ ነብዩ ኤልያስም ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር የዘጋውን ሰማይ ከፍቶት ዝናም እንዲዘንብ አደረገ፤ ሕዝቡንም ሰብስቦ ጣዖት የሚያመልኩም መጥተው መሥዋዕት እንዲሠው አስደረገ፤ ነገር ግን ያመልኩ የነበረው ራሳቸው ሰዎች የሠሩትን ጣዖት ነውና ጣዖቱ ጸሎታቸውን አልሰማቸውም፤ ነብዩ ኤልያስ ግን ገና የእግዚአብሔርን ስም ሲጠራ መሥዋዕቱን ተቀበለለት፤ በዚህም ለሕዝቡ የጣዖታትን ከንቱነት እንዲሁም የእግዚአብሔርን አምላክነት ተረድተው አመኑ፤ ንግሥት ኤልዛቤልም ይህንን ስትሰማ እያልን ልትገድለው ባለች ጊዜ ከፊቷ ፈቀቅ አለ፡፡ (ወደ ሌላ ቦታ ሄደ)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ነብዩ ኤልያስ በዘመኑ ብዙ ድንቅ ነገርን አድርጓል፤ ስለ እውነት ይመሰክር ነበር፤ ለተበደሉ ይከራከር ነበር፤ ለምሳሌ አንድ ጊዜ ኤልዛቤል የተባለችው ንግሥት ናቡቴ የተባለን ሰው አስገድላ መሬቱን ነጠቀችው፤ ነብዩ ኤልያስም ሳይፈራ ወደ ንጉሡ እና ሚስቱ በመሄድ ናቡቴን ገድለው መሬቱን መንጠቅ እንደሌለባቸው በማስገንዘብ ተናገራቸው፤ በዚህም ሊገድሉት አሳደዱት፤ እርሱ ግን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ሊገድሉት አልቻሉም፤ ነብዩ ኤልያስ ብዙ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ስለ እግዚአብሔር እያስተማረ፣ ሰዎች ከጣዖት አምልኮ እንዲወጡ እየመከረ ከኖረ በኋላ ከዚህ ምድር የሚለይበት ጊዜ ደረሰ፤ የእርሱ ደቀ መዝሙር ለነበረው ነብዩ ኤልሳዕ መጎናጸፊያውን ሰጠው፤ እግዚአብሔርም በእሳት ሠረገላ ጭኖ ወደ ብሔረ ሕያዋን (የቅዱሳን ሰዎች መኖሪያ) ወሰደው፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ነብዩ ኤልያስ ታሪኩ ብዙ ነው፤ በተለይ በመጽሐፍ ቅዱስ በመጽሐፈ ነገሥት ተመዝግቦ ይገኛል፤ እኛ ግን ለግንዛቤ እንዲሆናችሁ ጥቂቱን ታሪክ ነገርናችሁ፤ ብዙ ቁም ነገር እንደምትቀስሙ ተስፋ እናደርጋለን፤ ከነብዩ ኤልያስ ታሪክ የዓለማት ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደሆነ፣ ጣዖት ማምለክ እንደማይገባ፣ እንደ ኤልዛቤል በሰዎች ላይ ክፋት ማድረግ እንደማያስፈልግ፣ እንደ ነብዩ ኤልያስ ስለ እውነት መመስከር እንደሚገባ፣ በእግዚአብሔር መታመን፣ ጾመኛ፣ ጸሎተኛ፣ ለተበደሉና ለተቸገሩ መርዳት እንዳለብን እንማራለን፡፡

ነብዩን ኤልያስን ንጉሥ አክአብና ኤልዛቤል ሊገድሉት ሲሉ እግዚአብሔር ከእነርሱ ከልሎ በዋሻ ውስጥ አስቀምጦ አሞራ ምግቡን እንዲያመጣለት እንዳደረገ ሁሉ እግዚአብሔር ለሚታመኑት፣ ከልብ ለሚከተሉት፣ እውነትን ለሚናገሩና ለሰው ለሚያዝኑ እርሱም እንደሚረዳቸውም ተመልክተናል፤ ስለዚህም በሃይማኖታችን የጸናንና በምግባር የጎለበትን እንሁን! ሥነ ምግባር ያለው፣ ለወላጆች ታዛዥ፣ በሁሉ ነገር ጎበዝና፣ ንቁ ልጆች ልንሆን ያስፈልጋል!

የነብዩ ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ታኅሣሥ አንድ ቀን እና ጥር ስድስት ቀን ይከበራል፡።

🙏 አምላካችን እግዚአብሔር ከነብዩ ኤልያስ በረከቱን ያድለን፤ አሜን!

😇 Prophet Elijah (Kidus Elias)

In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) calendar, the Prophet Elijah (Kidus Elias) is honored, with his birth commemorated on the 1st day of the month of Tahisas (December 10th), a significant feast alongside the birth of the Virgin Mary (Lideta Mariam) and the Archangel Raguel. The EOTC celebrates his miraculous birth, where angels were seen around him, and his life as a great prophet who brought Israel back to God, eventually being taken to heaven in a fiery chariot.

Key Details:

  • Date: Tahisas 1 (December 10th).

  • Significance: A monthly feast day celebrating the birth of the Virgin Mary, Archangel Raguel, and Prophet Elijah.

  • Tradition: Celebrates Elijah's birth in Gilead to righteous parents, with angelic visions at his circumcision, and his life as a lamp to God's people, leading them from idolatry.

Elijah's Role in EOTC Tradition:

  • Prophet of Fire: Known for his fiery zeal for God and powerful miracles, like bringing rain.

  • Foregoer of Christ: Believed to be the one who will return before Christ's Second Coming, as prophesied in Malachi.

  • Ascension: Honored for being taken to heaven alive in a fiery chariot, appearing with Moses at the Transfiguration

According to Ethiopian Orthodox calendar The prophet Elijah was born on December 10 [Tahisas 1], in the province of Gilead, to his righteous parents, his father, Joshua, and his mother, Tonya, who had lived in the house of Levi. On the eighth day, when they had performed circumcision, they named him Elijah.

When the prophet Elijah grew up learning the Law, he left his mother, his father, his relatives, and all his money and lived in the wilderness. St. Paul in the Hebrews' message, "They went about in sackcloth, on carpets, and in goatskins; they were distressed, afflicted, afflicted, hungry, thirsty. These are the things that the world does not deserve: the forest goes for the mountain and the mountain, the cave for the caves and the crumbs for fear. " Hebrews 11:37

"Elijah" also means a lamp to the house of God, that olive oil might shine upon all that are in darkness. When the Israelites were in darkness when they broke into the law of God, worshiping idols, the prophet Elijah arrived and brought them back to God with a bright heart.

One of the great miracles the prophet had done with the power of God was to make rain and to revive again [1 Kings 17: 2]. The sacrifice of the Lord in the presence of the priest, and the disgrace of the priests [2 Kings 18: 38].

One day, as the prophet Elijah was praying, the Angel, the Holy Raguel was revealed and told him, "Rejoice, for the time has come for you to ascend to heaven. You will live in a land of complete happiness. A place where no sickness, death, sorrow, but full of blessing. There is one like you, Enoch, who writes the commandment of the Most High God.

"When the time came for God to bring Elijah to heaven, the prophet went from Gilgal to Jericho, and his disciple Elisha said, "By your living soul, I will not leave you." When they arrived in Jericho, there came small prophets from Jericho. Elijah's ascension was revealed to them by the wisdom of the Holy Spirit, and they said to Elisha, "Do you know that today the Lord will take away your Lord from you?" He said, "I know, keep quiet." Then Elijah went with Elisha, when he said, "Sit down here, for the LORD has sent me to the Jordan . I will not leave you."

Fifty men from the company of the prophets went and stood at a distance, facing the place where Elijah and Elisha had stopped at the Jordan. 8 Elijah took his cloak, rolled it up and struck the water with it. The water divided to the right and to the left, and the two of them crossed over on dry ground.

9 When they had crossed, Elijah said to Elisha, “Tell me, what can I do for you before I am taken from you?” “Let me inherit a double portion of your spirit,” Elisha replied.

10 “You have asked a difficult thing,” Elijah said, “yet if you see me when I am taken from you, it will be yours—otherwise, it will not.”

11 As they were walking along and talking together, suddenly a chariot of fire and horses of fire appeared and separated the two of them, and Elijah went up to heaven in a whirlwind. 12 Elisha saw this and cried out, “My father! My father! The chariots and horsemen of Israel!” And Elisha saw him no more. Then he took hold of his garment and tore it in two. 13 Elisha then picked up Elijah’s cloak that had fallen from him and went back and stood on the bank of the Jordan. 14 He took the cloak that had fallen from Elijah and struck the water with it. “Where now is the Lord, the God of Elijah?” he asked. When he struck the water, it divided to the right and to the left, and he crossed over. [2 Kings 6-14]

As Elijah crossed the Jordan River into the living nations, the believers born of the water and the Holy Spirit will inherit the kingdom of God. Our Lord said in the Gospel of John that "a person who is not born again cannot see the kingdom of God."

The prophet Elijah was one of the fifteen prophets (Moses, Joshua, Samuel, Jonathan, Gad, David, Solomon, Elisha, Ezra, Isaiah, Daniel, Jeremiah, Ezekiel, and John the Baptist). This is a prophet who spoke physically with our Lord on the Mount of Tabor, a priest who broke down the sacrifice of idols, a traditional priest who initiated the ordinance;

Our Lord, our Savior, Eyesus Kirstos, has called John "Elijah" when he witnessed the greatness of the Holy Spirit of baptism. Our Lord calls John “Elijah” because it implies that he is teaching ahead of the Second Coming of Eyesus Kirstos,

James 5:17: "Elias was a man subject to like passions as we are, and he prayed earnestly that it might not rain: and it rained not on the earth by the space of three years and six months."

🙏 May the prayers of Prophet Elijah and St, Raguel the Archangel of JUSTICE be up on us!


Friday, November 21, 2025

ህመምተኞች በንቡ የሚፈውሱበት ተዓምረኛው "ንቡ ቅዱስ ሚካኤል" ቤተ ክርስቲያን

በአክሱማዊቷ ኢትዮጵያ ላይ ጠላቶቿ የዘር ማጥፋት ጂሃድ ከመክፈታቸው በፊት…

🐝 “ንቡ ሚካኤል” በአዲስ አበባ፡ 'አያት' የሚባለውን ቦታ አለፍ ብሎ በሻሌ ኮረብታ ላይ የሚገኝ ቤተክርስቲያን ነው። ወደዚህ ቤተክርስቲያን እንዴት እነደመጣሁ ሁሉ አላውቅም፤ ቅዱስ ሚካኤል ነው ያመጣኝ።

የንቡ ቀፎ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ ነው ያለው። የንቡም መንጋ ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል። በቅዳሴ ሰዓትና ታቦት በሚወጣበትም ጊዜ ሁሉ ቤተክርስቲያኑ ውስጥ ንቡ ይወጣል። በንብ የሚነደፍ ከተለያዩ በሽታዎች ይፈወሳል። ንቦቹ ዝም ብለው አይናድፉም፤ የተፈቀደለት ሰው ነው ሊነደፍ የሚችለው። ይሄን እንደሰማሁ በጣም ተደስቼ "ጢናማ ያደረገኝ ቸሩ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ዶክተር ካየሁ ሃያ ዓመት ገደማ ሆኖኛል ፥ ግን ሳጥናኤል አገር እየተኖረ ጋኔን መግቢያ ቀዳዳ አያጣምና በቃ ንቦቹ በውስጤ ሊኖር የሚችለውን መርዝ ነቅለው ሊያወጡልኝ ነው ብዬ ቤተክርስቲይኑን መዞር እንደጀመርኩ ከየት እንደመጣ ያላየሁት አንድ ጎረመሳ ልጅ አብሮኝ ይዞር ጀመር(አልፎ አልፎ ቪዲዮው ላይ ይሰማል)“ከየት መጣህ? ትምህርት ቤት የለህም እንዴ? እንዴት ወደዚህ ብዙ ሰው ወደ ሌለበት ቦታ መጣህ?" ብዬ ጠየቅኩት። እርሱም፡ "አይ መንገድ ላይ ከጓደኞቼ ጋር በመኪና መጥተን ተጠፋፋን፣ ከዚያም እኔ ዝም ብዬ ወደዚህ መጣሁ" አለኝ። ትህትና ያለው ስለነበር አመንኩት። ንቦቹ ቢነድፉኝ በማለት ቤተክርስቲያኑን መዞሩን ቀጠልኩ ግን አሁንም አብሮኝ ይዞራል። በቃ ስላልተነደፍኩ ራመድ ብዬ ከአንዲት ሱባኤ ከያዙና ደስ ከሚሉ እናት ጋር ማውራት ጀመርኩ። ስለቤተክርስቲያኑ በይበልጥ ማወቅ ከፈለግክ በጥቅምት ተመልሰህ ና፤ ያኔም ማር ይቆረጣል ፈውስ ነው ይዘህ ትሄዳለህ አሉኝ። እኔም ከምስጋና ጋር በጥቅምት ስለምጓዝ እንደማልችል አሳውቂያቸውና ተሰናብቻቸው ድንቅ የሆነ ቦታ ላይ ካለው የቤተክርስቲያን ግቢ ወጣሁ። አሁንም ያ ጎረምሳ ተከትሎኝ መጣ፤ "እስኪ ባክህ ወደ አያት የሚወሰደው ታክሲ የሚቆምበትን ቦታ አሳየኝ" አልኩት፤ " ቦታውን ካሳየኝ በኋል ሞባይሉን አውጥቶ መደወል ጀመረ። መንገዱ በጣም ጭር ያለ ነው፣ መኪናም ብዙ የለም። በዚህ ጊዜ ከአውቶብስ ማቆሚያው ፊት ለፊት አንድ የስልክ ምሰሶ ላይ ነጭና ጥቁር ቀለም ያለው ቁራ ወደ እኛ አቅጣጫ ሲጮህ ይሰማል። በጣም የሚገርም ነው፤ "ጉሮሮው እስኪወጣ" ድርስ በኃይል ነበር የሚጮኸው። "ምን እያለን ይሆን?” አልኩት ለልጁ፡ በዚህ ሰዓት መልስ ሳይሰጠኝ ፊቱ ሲለዋወጥ አየሁት። በዚህ ጊዘ አንድ ታክሲ ከች አለ። እንደገባሁ ታክሲው በቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል ስዕሎች የደመቀ ነበር። "ዋው! ቅዱስ ሚካኤል በቁራው በኩል ስለሆነ ነገር እያስጠነቀቀኝ ነበር" አልኩ፤ በጣም በመገረምና በመደሰት።

ከሁለት ቀን በኋላ፡ ማታ ላይ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን አካባቢ ሦስት ቻይናዎች ወደ ዘረጓቸው እጆቻቸው ሞባይላቸውን አብርተው አየሁና "እንግሊዝኛ ትችሉ ይሆን ምን ችግር ገጠማችሁ?” አልኳቸው። እነርሱም በጠራ እንግሊዝኛ "እጃችንን ቢንቢዎችን ልናስነክስ ፈልገን ነው፤ ቢንቢዎች ጎጂ ባክቴሪያዎችን ያጠፉልናል፤ እዚህ አገር አየሩ ቆንጆ ስለሆነ ጤናማ ቢንቢዎች ናቸው" አሉኝ። ቻይኖቹ ትክክል ናቸው፤ በቅድስት ኢትዮጵያ ንቦቹና ቢንቢዎቹ መድኃኒቶቻችን ናቸው፣ አዕዋፋቱና እንስሳቱ ረዳቶቻችን ናቸው። ቸሩ እግዚአብሔር ለሕዝባችን ሁሉንም ነገር በነፃ አዘጋጅቶለት ሳለ፡ ከወጣት እስከ አዛውንቱ ለቀላል በሽታ የፈረንጁን ኪኒንና መርፌ በውድ ገንዘብ ሲሸምት ሳይ በጣም አዝናለሁ።

በአውሬው መዳፍ ሥር የሚሰቃዩትን ወገኖቻችንን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዕለተ ቀኑ ይድረስላቸዉ ካሉበት መከራና ስቃይ በምልጃው ያውጣቸው! የእግዚአብሔርን ሕዝብ ከመከራ ታዳጊ ቅዱስ ሚካኤል ነውና የሃገራችን ጠባቂ የሊቀ መልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከቱ ከሁላችን አይለየን!!!

ተ ዓምረኛው በሻሌ ንቡ ቅ/ሚካኤል እና ሰማዕቱ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን

የእግዚአብሔርን ሥራ በምድር ያደረገውን ታምራት እንድታዩ ኑ” (መዝ. ፵፭፥፰)

🐝 በንብ መንጋ የተከበበው የበሻሌ(ንቡ) /ሚካኤል፣ ቅ/እስጢፋኖስ እና ወአባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ቤተክርስቲያን አመሰራረትና ገቢረ ተዓምራት አጭር መግለጫ፤

ቤተክርስቲያኑ ከመመስረቱ በፊት በቦታው ላይ ሲከናወኑ የነበሩ ልዩ ልዩ ተዓምራት፡-

. ለብዙ ዓመታት ከተለያየ ቦታ ተጣልተው የነበሩ ምዕመናን ቦታው ላይ እየመጡ እርቀ ሰላም ሲፈጽሙበት ኖረዋል፤

. ቤተክርስቲያኑ ከተተከለበት ቦታ ትልቅ የጽድ ዛፍ ላይ የሚወጣው ሙጫ እንደ እጣን ጢስ ሽታ ለብዙ ዓመታት አካባቢውን መዓዛው (ሽታው) ያውድ ነበር፡፡

. በዚሁ ቦታ ላይ ሌሊት ሌሊት የመላዕክት ዝማሬ (ጣዕመ ዜማ) የከበሮ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ በዕድሜ የገፉ የአካባቢው አዛውንቶች ተናግረዋል፡፡

. በአካባቢው ከሚኖሩ ምዕመናን መካከል በመልካም ስራቸው የታወቁና ከዘጠና/90 ዓመት በላይ ዕድሜ የነበራቸው እናት የቅዱስ ሚካኤል ታቦት(ጽላት) እንደሚተከል በተደጋጋሚ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ይናገሩ ነበር፡፡

. ቀደም ሲል በእነ አብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት አካባቢ ጀምሮ ከተለያየ አካባቢ የሞቱ አባቶች አስከሬናቸው እየመጣ ሥርዓተ ቀብር ሲፈጸምበት የቆየ እና በተለያየ ጊዜ የቀስተ ደመና ብርሃን በመቃብሩ ላይ ይታይ እንደነበር በአካባቢው የሚኖሩ በዕድሜ የገፉ አዛውንቶች በግልጽ መስክረዋል፡፡ ዛሬም መቃብሩ በግልጽ ይታያል፡፡ ይህ ሁሉ ታሪክ ሲከናወን ከቆየ በኋላ እግዚአብሔር የፈቀደው ጊዜ ሲደርስ በአካባቢው ከሚኖሩ በዕድሜ ከገፉ አዛውንቶች መካከል በአንድ አርሶ አደር ምዕመን አማካኝነት በእግዚአብሔር ፈቃድ በተደጋጋሚ ራዕይ ተገልጾላቸው ያርሱበት የነበረውን ይዞታቸውን መሬት ለዚህ ታቦት መትከያ ቤተክርስቲያን እንዲሰራ መሬት በመስጠት አሁን በሚገኘው መቃኞ ቤተክርስቲያን ግንቦት 12 ቀን 2001 .ም ታቦቱ ሊገባ ችሏል፡፡

በቤተመቅደሱ ስለሚገኘው የንብ መንጋ አገባብ (አመጣጥ)

😇 እግዚአብሔር አስቀድሞ ቦታውን ስለመረጠው፡-

. ሕዳር ፲፪/12 ቀን ፳፻፪/2002 .ም የቅዱስ ሚካኤል በዓል ሲከበር በዋዜማው ሊቃውንቱ በአገልግሎት ላይ እንዳሉ ማለትም ሕዳር ፲፩/11 ቀን ፳፻፪/2002 .ም ከቀኑ 900 ሰዓት ገደማ ከምስራቅ አቅጣጫ የንብ መንጋ መጥቶ የቃል ኪዳኑ ታቦት በሚገኝበት በመንበሩ ውስጥ ገብቶ ካደረ በኋላ በነጋታው ታቦቱ ወጥቶ በሚከበረበት ጊዜ ንቡ ከመንበሩ ወጥቶ እንደ ደመና ረቦ ካሉት ምዕመናን ጋር ታቦቱን ዙሮ አክብሯል፡፡ በዕለቱም ይህን አስደናቂ ታምር ያዩና የተመለከቱ ምዕመናንም በከፍተኛ ድምጽ እግዚአብሔርን አመስግነዋል፡፡

. ሕዳር ፲፩ /11ቀን ፳፻፬/2004 .ም የድንግል ማርያም ዕለት ካህናቱ ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጉልላት ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ አስራ አድን/1100 ሰዓት ላይ ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ቤተልሔም ውስጥ ገብቶ እስከአሁን ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

. ታህሳስ ፱/9 ቀን ፳፻፬/ 2004 .ም ከቀኑ ዘጠኝ/900 ሰዓት የንብ መንጋ መጥቶ ከቤተክርስቲያኑ ጎን ላይ ከሰፈረ በኋላ ከቀኑ አሥራ አንድ ሰዓት ተኩል/ 1130 ተነስቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ወደ ግብር ቤት ገብቶ እስከአሁን

ድረስ ሰፍሮ ይገኛል፡፡

. ታህሳስ ፲፱/19 ቀን ፳፻፭/2005 .ም የቅዱስ ገብርኤል ዕለት ካህናት ቅዳሴ ገብተው በሚቀድሱበት ጊዜ ቅዱስ ወንጌል ሲነበብ የንብ መንጋ መጥቶ በሴቶች መግቢያ በር ወደቤተክርስቲያኑ ከገባ በኋላ በቀጥታ ወደ ቤተመቅደሱ ውስጥ ገብቶ በአጎበሩ ላይ ሰፍሯል፡፡ ይህ በቤተክርስቲያናችን ላይ ያለው የንብ መንጋ ማሩ ተቆርጦ በተለያየ ጊዜ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ተሰጥቶ ከአገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በጉበት፣ በካንሰር፣ በኪንታሮት፣ በስኳር፣ በአስም፣ በጨጓራ፣ በኩላሊት፣ በደም ግፊት፣ በኤች አይ ቪ፣ ሽባዎች፣ አይነስውራን፣ አፈ ዲዳዎወች፣ መስማት የተሳናቸው፣ በጭንቀትና በልዩ ልዩ በሽታ የታመሙ ሰዎች ማሩን በልተው ጸበሉን ጠጥተው እምነቱን ተቀብተው ከበሽታቸው ተፈውሰው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡ እንዲሁም ለብዙ ዓመታት ልጅ አጥተው የነበሩ ሰዎች (መካኖች) በአንድ ጊዜ ሁለት ልጆች መንታ እንዲሁም በአንድ ጊዜ ሶስት ልጆች መንታ ወልደው

ታቅፈው መጥተው ጥምቀተ ክርስትናቸውን በዚሁ ቤተክርስቲያን እንዲፈፀም ማድረጋቸውና ሌሎች በዚህ አነስተኛ ጽሁፍ ሊገለፁ የማይችሉ በርካታ ገቢረ ተዓምራትና ፈውሶች እስከአሁኗ ሰዓት እየተደረጉ ናቸው፡፡

ክብርና ምስጋና ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን አሜን፡፡

😇 በእግዚአብሔር ፈቃድ በንቦቹ የተደረጉት ተዓምራት በከፊል

. ሕዳር ፲፪/12 ቀን ፳፻፪/2002 .ም የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ በሚከበርበት ጊዜ ከቤተመቅደሱ ያለው ንብ ወጥቶ ታቦቱን አክብሯል፡፡

. ፳፻፫/2003 .ም የስቅለት በዓል ሲከበር ንሴብሆ እየተባለ በሚዘምርበት ጊዜ ንቡ ወጥቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ገብቷል፡፡

. መጋቢት ፲፪/12 ቀን ፳፻፬/2004 .ም የቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ በዓል ቅዳሴ እየተቀደሰ ሳለ የቤተመቅደሱ ንብ ከመንበሩ ላይ የመስቀል ምልክት ሰርቶ (ሰፍሮ) ታይቷል፡፡

. ሕዳር ፲፩/11 ቀን ፳፻፭/2005 .ም ንቡ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባበትን ዕለት ለማስታወስ ከቀኑ 400 ሰዓት ላይ ንቡ ወጥቶ ቤተክርስቲያኑን ዙሮ ገብቷል፡፡

. ፳፻፭/2005 .ም ፀሎተ ሐሙስ የሕጽበተ እግር ጸሎት ሲከናወን የመቅደሱ ንብ ወጥቶ ፀበሉ ላይ ሰፍሮ (ረቦ)ታይቷል፡፡

. ፳፻፮/2006 .ም እሁድ የሆሳዕና በዓል ሲከበር ሆሳዕና በአርያም እየተባለ እየተዘመረ ዑደት በሚደረግበት ጊዜ ብዙ ምዕመናን ባለቡት የቤተመቅደሱ ንብ ወጥቶ ዞሮ ገብቷል፡፡ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል፡፡ ለዘላለሙ አሜን፡፡

📦 በቤተክርስቲያኑ ላይ የቃል ኪዳኑ ታቦት የሚነግስበት ቀናት፤

. ሕዳር ፲፪/12፣ ጥር 12፣ ግንቦት 12 ቅዳሴ ቤቱ፣ ሰኔ 12 ቀን የመልዓኩ የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በየዓመቱ ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡

. ጥቅምት ፲፯/17 እና ጥር ፩/1 ቀን የሰማዕቱ የቅዱስ እስጢፋኖስ ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡

. ታሕሳስ ፲፰/18 እና ሐምሌ ፳፮/26 ቀን የጻድቁ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ዓመታዊ በዓል ታቦቱ ወጥቶ ይነግሳል፡፡ በእነዚህ የንግስ በዓላት ላይ ከቤተመቅደሱ የተቆረጠው ማር ለመድኃኒትነት ይሰጣል፡፡

😇 የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ እና የጻድቁ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን ፡፡

😇 የገናናው መልአክ የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃው አይለየን፣ በጸሎቱ ይማረን።

Monday, October 27, 2025

Saint Stephen’s Martyrdom in an Ancient Manuscript | የቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት በጥንታዊ ጽሑፍ

https://www.bitchute.com/video/iPau2wt5fzzF/

https://rumble.com/v70us8k-saint-stephens-martyrdom-in-an-ancient-manuscript-.html

እስጢፋኖስ በግሪክ ቋንቋ አክሊል ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው

ቅዱስ እስጢፋኖስ በቤተክርስቲያን ታሪክ ስለክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ዲያቆን ነው

ቀዳሚ ሰማእት / እስጢፋኖስ በጥቅምት ፲፯ ዕለት ሊቀ-ዲያቆናት ተደርጎ በሐዋርያት ተሾመ፡፡

😇 ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ የተቀዳጃቸው ሦስቱ አክሊላት፡-

    . ስለንፅህናው ስለድንግልናው

    . ስለሰማዕትነቱ /ስለምስክሩ/ ስለተጋድሎው

    . ስለስብከቱ /ስለትምህርቱ/ ስለተአምራቱ

ቅዱስ እስጢፋኖስ የተወገረበት ድንጋይ ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ታንፆበታል፡፡ /ሰባት ቤተክርስቲያናትን አንጿል፡፡/

የቤተክርስቲያን አባቶች የቀዳሜ ሰማዕት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት ለክርስትና እምነት መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት መሆኑ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራውን እንድናይበት አድርጎናል ሲሉ ይገልፁታል እውነት ነውና፡፡

የቀዳሚ ሰማእት የቅዱስ እስጢፋኖስ ሞት ለክርስትና እምነት መስፋፋት ዋነኛ ምክንያት ነበር፤ የዘመኑ የወገኖቻችን ሰቆቃ እና ሞትም ለተዋሕዶ ክርስትና መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

🙏 እንኳን አደረሰን! ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በረከቱን ያድለን አሜን !!!

😇 Archdeacon and First Martyr Saint Stephen

In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, Saint Stephen is commemorated monthly on the 17th day of every month, and the annual feast of Saint Stephen the Archdeacon is celebrated on Teqemet 17 (which is October 27th in the Gregorian calendar). He is honored as the first martyr (Protomartyr) and as the first of the seven deacons chosen after Pentecost

Dedication to the ordination of the First Martyr and Archdeacon Stephen, who was stoned to death about three years after the Ascension of the Lord.

Saint Stephen was a Hellenistic Jew and belonged to the group of the seven deacons selected by the Apostles to carry out the charity work of the first Christian community of Jerusalem.

According to the Acts of the Apostles, he was a man filled with the grace of the Holy Spirit. He preached with boldness and performed many great wonders. His action caused the animosity of the Judean priesthood, for they failed to understand and accept the ecumenical dimension and the liberating content of Christ’s preaching to every human being, and especially to those who had been wronged.

The First Martyr Stephen was considered a blasphemer and a denier of Judaism, for he declared, even before the Sanhedrin (great assembly), that Moses and the Mosaic Law, as well as all the Prophets and the Righteous of the Old Testament, were not carriers of salvation, but prepared the way for the coming of the true Savior, who is Christ.

Imitating His love, and dedicating himself to Him, he forgave his murderers, begging the Triune God not to impute to them the sin they had committed.

🙏 May his intercession be with all of us, Amen!

ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አቡነ እየሱስ ሞዐ አንድነት ገዳም፤ ቀዳማይ ዩኒቨርሲቲ ዘኢትዮጵያ

https://wp.me/piMJL-bJo

የሐይቅ እስጢፋኖስ /አቡነ እየሱስ ሞዓ አንድነት/ ገዳም

መስቀል፤ የመስከረም ፲፯ / ፳፻፲፩ ዓ.ም ክብረ በዓል በቅዱስ እስጢፋኖስ | የሰዶም ዜጎች አዲስ አበባን ገና ሳይቆጣጠሯት

https://wp.me/piMJL-dHW

(ይህን ጦማሬን እስካሁን ድረስ አፍነውታል፤ በየረርና የካ ተራሮች በዋሻ ሚካኤል እና በአክሱም ላሊበላ ተራራማ ዋሻዎች ላይ እየተሠራ ያለውን የሉሲፈራውያኑን ሤራ በከፊል በማጋለጡ!)

💭 በወቅቱ የቀረበ ጽሑፍ ፥ ትናንትና ዛሬ፤ በትናንትናው የመስቀል አደባባይ የኢሬቻ ጣዖት አምላካዊች የጽዮንን ሰንደቅ ከለከሏቸው፤ ዋይ! ዋይ! ዋይ!

የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያንን ግቢ እንዲህ ግጥም፡ ሙልት ብሎ አይቼው አላውቅም፤ በአረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማታችን ያሸበረቁ በጣም ብዙ ምዕመናን ተገኝተው ነበር።

ለመንፈሳዊ ሕይወት በጣም ታታሪ የሆነው ክርስቲያን ወገናችን ሊመሰገን፣ ሊወደስና ሊደነቅ ይገባዋል፤ ብዙ ጊዜ ሲኮነን እንጂ ሲደነቅ አንሰማም። ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት አንስቶ እስከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ድረስ ቀዳሚ ሰማዕት ቅ/እስጢፋኖስን ለማስታወስ በቤተክርስቲያኑ ተገኝቷል።

እስኪ የት ሌላ ዓለም ነው ተመሳሳይ ሁኔታ የሚታየው? በየትኛውስ ሌላ ሐይማኖት? ካቶሊኩና ፕሮቴስታንቱ ከአንድ ሰዓት በኋላ፣ እስላሙ ከሠላሳ ደቂቃ በኋላ ነው ለአምላኮቻቸው ጸልይው የሚበታተኑት።

ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን፣ ለመጀመሪያ ጊዜ በንግሥት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በ፲፱፻፱ ዓ/ም ተመሠረተ። በዚያን ጊዜም ዘመኑ በፈቀድው መልክ የቤተ ክርስቲያኑ ሕንጻ ተጠናቆ ሲወደስበት ሳለ፤ በጣልያን የወረራ ዘመን፣ በ፲፱፻፴፪ ዓ/ም ባልታወቀ ምክንያት የእሳት አደጋ ደርሶበት ሕንጻው ተቃጠለ።

ኢትዮጵያ ከ ፋሺስት የወረራ ቀንበር ከተላቀቀች በኋላ፤ የግንባታው ሥራ በሥራ ሚኒስቴር ኃላፊነት በዘመናዊ መልክ እንዲሠራ በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ሚኒስትሩ ባላምባራስ (በኋላ ብላቴን ጌታ) ማኅተመ ወልደ መስቀል በአንድ በኩል የአካባቢውም ኗሪ እና የቤተ ክርስቲያኑ ምእመን በመሆናቸው እና በሚኒስቴራዊ ኃላፊነታችው፤ ሥራውን በቅርብ እየተከታተሉና እየተቆጣጠሩ አሠርተውት የአሁኑ ሕንጻ ግንባታ ፍጻሜ አግኝቶ ጥቅምት ፲፯ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ/ም ቅዳሴ ቤቱ የግብጽ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን ፓትረያርክ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ፮ኛ በተገኙበት ተባረከ፡፡



Friday, September 26, 2025

Meskel: The Feast Day Which Marks the Discovery of The True Cross of Jesus Christ


https://www.bitchute.com/video/3YIl9lLbY4GW/

https://rumble.com/v6zi21w-meskel-the-feast-day-which-marks-the-discovery-of-the-true-cross-of-jesus-c.html

መስከረም ፲፮/16 ቀን ደገኛዋ እናት እሌኒ ቅድስት ደመራ ደምራ በደመራው ጢስ አማካኝነት

የተቀበረበትን ቦታ አገኘች መስከረም ፲፯/ 17 ቁፋሮ ጀመረች፤ ከ ፫፻/300 ዘመናት በላይ ቆሻሻ እየተጣለበት ታላቅ ተራራ አህሎ ነበርና እነሆ ቁፋሮ ስድስት ወራት ፈጀባቸው መጋቢት 10 በዛሬዋ ቀንም መስቀሉ ወጣ።

ሦስት መስቀሎች ናቸው፤ ሁለቱ መስቀሎች ሽፍታዎቹ የተሰቀሉባቸው ሲሆኑ አንዱ የጌታችን ነው፤ ታዲያ እንዴት ለየችው ቢሉ የጌታችን መስቀል ታላላቅ ተዓምራትን አድርጓል ድውይ ፈውሷል ዓይ ነስውር አብርቷል።

ይህንን ቀን ቅድስት ቤተክርስቲያን "መስቀለ እየሱስ" ስትል ታከብረዋለች፤ በዛሬዋ ቀን ዝማሬው፤

ምስጋናው፤ ትምህርቱ፤ ቅዳሴው ፤ ንባቡ ሁሉም መስቀልን የሚመለከቱ ናቸው።

እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት የእውነተኛው መስቀል ግኝት በመጋቢት ወር ነው ተብሎ ቢታመንም መስቀል ግን በዐቢይ ጾም ወቅት በዓል እንዳይከበር ወደ መስከረም ተወስዷል።

😇 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለ መስቀል የሚጣፍጥ ነገር ተናገረ እንዲህ ሲል፤

❖❖❖[ወደ ገላትያ ሰዎች ምዕራፍ ፮፥፲፬]❖❖❖

ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።”

Tonight and tomorrow we Ethiopian Orthodox Christians celebrate The Feast Day which marks the discovery of The True Cross of Jesus Christ.

The discovery of this revered relic within Christianity can be traced back to the fourth (4th) century when the mother of the Roman Emperor Constantine, Queen Helena received divine guidance to its location.

According to legend, Queen Helena, now canonized, had a dream. In the dream, she was told to make a bonfire from which the smoke would show her the location where the True Cross of Jesus was buried.

After doing as she was instructed and the bonfire lit, the smoke rose high up to the sky and returned to the ground, exactly where the Cross had been buried. Thus began the yearly celebration of the discovery.

According to the Ethiopian Orthodox Church, the discovery of the True Cross is traditionally believed to have been in March, but Meskel was moved to September to avoid holding a festival during Lent, and because the church commemorating the True Cross in Jerusalem was dedicated during September.

❖❖❖[Galatians 6:14]❖❖❖

But far be it from me to boast except in the cross of our Lord Jesus Christ, by which[a] the world has been crucified to me, and I to the world.”

መስቀሉን ይዘን ተሸክመን እናት ኢትዮጵያን ከሉሲፈራውያኑ እና ጭፍሮቻቸው የሞትና ባርነት ቀንበር ቶሎ ነፃ እናውጣት!

https://wp.me/piMJL-dHo

መስቀል ጋሻና ጦር ይዘህ ለመርዳት ተነሳ፣ መስቀል ሰይፍህን መዘህ የዘበቡኝን ከበባቸው!

🔥 አለም ወደ ኑክሌር ጦርነት እየተንደረደረ ነው፤ እነሱ ኒውክሌር ሊያብላሉ ሲቆፍሩ እኛ እኮ ከተቆፈረበት በተዓምር የወጣ ግማደ መስቀሉን ይዘን ነበር


  • የበዓል ስም ፤ በመስከረም ፲፯ ቀን የሚከበር ታላቅ በዓል ፤ የመስቀል ቅዳሴ ቤቱ።

  • ጌታ በሰቀለበት አምሳል ከንጨት ከብረት ከብር ከወርቅ ከንሓስ ከእብነ በረድ ከሌላም ማዕድን የተሠራ ቄሶች በእጃቸው የሚይዙት ክርስቲያኖች ባንገታቸው የሚያንጠለጥሉት ፤ ሴቶችም በቀሚሳቸው ላይ ያስጠልፋታል። (ያበባ መስቀል) ፤ ካበባ የተጐነጐነ እንቍጣጣሽ።

  • ግንባር ማማተቢያ ጣት የሚያርፍበት ፤ ወይም የመስቀል ምልክት ዕመት የሚደረግበት። እረኛው ላውሬ የወረወረው ደንጊያ አቶ እከሌን መስቀሉን አለው ።

  • የክርስቶስ መስቀል በኹለት ረዣዥም ዕንጨት እጅና እግሩ የተቸነከረበት ከራሱ እስከ እግሩ ወራጅ ግንድ ከቀኝ እጁ ወደ ግራ እጁ ከአግዳሚውም ግንድ ባራት ማዕዘን ተመሳቅሎ የሚታየው መስቀልኛ ዕንጨት።

  • ሐዋርያ መስቀል ትርፍ ነገር ትርፍ ቅርጽ የሌለው ልሙጥ መስቀል።

  • ሕማማተ መስቀል የክርስቶስ ልዩ ልዩ መከራው በጥፊ መመታቱ መታሠሩ መገረፉ ግንድ መሸከሙ ራቁቱን መሰቀሉ አክሊለ ሦክ የሾክ አክሊል በራሱ ላይ መቀዳጀቱ ይኸንን የመሳሰለ ልዩ ልዩ መከራው ሕማማተ መስቀል ይባላል።

  • ልዩ ልዩ መስቀል የመስቀል ዐይነት ኹኖ በልዩ ልዩ አቀራረጽ በልዩ ልዩ ሥራ ተሠርቶ የሚታየውን በየሥዕሉ ማሳየት።

  • ቀራንዮ መስቀል በቀራንዮ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዋነኛው የቀራንዮ መስቀል።

  • ቀርነ በግዕዝ መስቀል እንደ በግ ቀንድ ኹኖ በተሠራው መስቀል በመጽሐፍ ድጕሰት ላይ የሚታይ ቆለፍ ቆለፍ ያለ።

  • ትእምርተ መስቀል የመስቀል ምልክት ወይም መስቀልኛ።

  • ነገረ መስቀል የመስቀልን ነገር መነጋገር መሥራት ማሳየት።

  • ዕርባን ሥራ መስቀል ብሩ ወርቁ በልዩ ልዩ አቀራረጽና ንቅስ ተነቅሶ በሙሻ ዘርየሚሠራ ዕርባን ሥራ ንቅስ መስቀል።

  • ዕርፈ መስቀል ማንካ ቀሳውስት ለሚቆርቡ ምዕመናን ደሙን የሚያቀብሉበት ማንካ በቤተ ክርስቲያን የሚኖር ዕርፈ መስቀል ይባላል።

  • የመስቀል አበባ በዘመነ ጽጌ የሚፈነዳው አበባ እንደ መስቀል ቅርጽና መልክ ያለው የመስቀል አበባ ይባላል።

  • የመስቀል ዎፍ ጥቍር ሰማያዊ የምትመስል በመስከረም በመስቀል በዐል ብቅ የምትል ድንቢጥ የመስከረም ዎፍ ትባላለች።

  • የመስቀል ደመራ በመስከረም ፲፮ ቀን ለመስቀል ዋዜማ ሕዝብ ኹሉ ርጥብ ዕንጨትን እያመጣ የሚደምረው ደመራ።

  • የመስቀል ጥቢ የመስከረም መስቀል ዘመን መስቀል ከዋለ በኋላ መስቀል ጥቢ መባል (ሰቀለ ሰቀለ መስቀል ([ግዕዝ])

  • የመስከረም መስቀል እሌኒ ንግሥት በመስከረም አስጀምራ ያስቆፈረችው በመስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን የሚውለው በዐል ነው።

  • የመጋቢት መስቀል በመጋቢት ዐሥር ቀን የሚውለው የመስቀል በዐል ነው።

  • የሰሎሞን መስቀል የሰሎሞን የሊሻኑ ዐይነት መስቀል።

  • የስቅለት ማግስት ከስቅለት በማግስት የሚውለው ቅዳሜ ሹር።

  • የስቅለት ዕለት ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል።

  • የተመሰቃቀለ መንገድ ዐራት ወገን ዐምስት ወገን ስድስት ወገን የሚያስኬድ አቋራጭ መንገድ።

  • የዐላማ መስቀል ለሃይማኖት ምልክት በዐላማ ላይ ለሚሰፋ የመስቀል ምልክት ወይም በሰንደቁ ላይ የሚታየው የዐላማ መስቀል።

  • የአንገት መስቀል እንደ ዕርባን ሥራ ወይም ልዩ ልዩ ሥራ ኹኖ ለአንገት እንዳይከብድ ትንሽ ኹኖ የሚሠራ መስቀል።

  • የዐጤ መስቀል በመስከረም ዐሥር ቀን ካህናት በቤተ መንግሥት ተሰብስበው ርእዩ ዘገብረ እግዚእነን ... አመልጥነው ተቀጸል ጽጌ እገሌ ሐፄጌ (ኅይለ ሥላሴ ሐፄጌ) እያሉ ወይም በእየ ጊዜው የነገሠዉን ንጉሥ የሚያወድሱበት ቀን ያጤ መስቀል ይባላል።

  • የእጅ መስቀል ጳጳሳት ኤጲስ ቆጶሳት ቀሳውስት በእጃቸው አዘውትረው የሚይዙት መስቀል።

  • ፀዋትወ መስቀል ([ግዕዝ]) ከመስቀል ወገን የኾነ መከራ ወይም የተቀደሱ የመስቀል ዕቆች።

Luciferian Agent PM of The Fascist Oromo Islamic Regime of Ethiopia Again Used the Language of Genocide

https://www.bitchute.com/video/48xFHBUk706F/ https://rumble.com/v72xiju-luciferian-agent-pm-of-the-fascist-oromo-islamic-regime-of-ethiopia...