https://www.bitchute.com/video/zpZ0pSXPYmiC/
😇 አንድ ቀን ነብዩ ኤልያስ ጸሎት እያደረገ ሳለ መልአኩ ቅዱስ ራጉኤል ተገልጾ፡-
"ኃላፊ፣ ጠፊ የኾኑ ሕሊናትን ያሸነፍህ፤ ሞትንም ድል ያደረግህ ተጋዳይ ሆይ ፈጽሞ ደስ ይበልህ፡፡ ወደ ሰማይ የምታርግበት ዘመን ደርሷልና፡፡ ፍጹም ደስታ፣ ፈገግታ፣ ተድላ ከሰፈነበት አገር ትኖራለህ፡፡ ደዌ፣ በሽታ፣ ሞት፣ ኀዘን ከሌለበት፤ በረከት፣ ከሞላበት ቤትም ትገባለህ፡፡ በዚያም የልዑል እግዚአብሔርን ትእዛዝ የሚጽፍ እንደ አንተ ያለ ሄኖክ አለ፡፡ አሁንም ተነሥና ዮርዳኖስን ተሻግረህ ሒድ" አለው፡፡
ደመና ደመና ….. በሠረገላ፤
ኤልያስ ኤልያስ ….. በሠረገላ፤
በእሳት ሠረገላ ….. በሠረገላ፤…
ሰወረው ደመና ….. በሠረገላ፤
ኤልያስ ያረገው… በሠረገላ፤
በእሳት ሠረገላ…. በሠረገላ፤
በጾም በጸሎት ነው …. በሠረገላ፤
አይደለም በሌላ …. በሠረገላ፡፡
እንኳን ለ ለታላቁ ነብይ ለቅዱስ ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል (የልደት ቀን)አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት ከነብዩ ኤልያስ፣ ነብዩ ሔኖክ፣ ከፓትርያርክ አባታችን ቅዱስ ሔኖክ፣ ከቅዱስ ራጉኤልና ቅዱስ ጴጥሮስ ጋር በተያያዘ ተዓምር ልላቸው የምችላቸውን አስገራሚ ክስተቶች እየታዘብኩ ነው። በዚህች ምድራችን ላይ ብቻ ሳይሆን በተለይ ፀሐይ ላይ የሆነ ዓለምን ሊለውጥ የሚችል ክስተት በእነዚህ ቀናት እየታዘብን ነው። ከእነ ነብያቱ ሔኖክ እና ኤልያስ መምጣት ጋር የሚገናኝ ክስተት ይሆን? የሆነ ትልቅ ነገር ይሰማኛል!
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉት ቅዱሳን ነብያት ዝናም በማቆም ብቸኛው ነብይ ቅዱስ ኤልያስ በዘመነ ነገሥታት ከነበሩ ነቢያት አንዱ ነው፤ አባቱ ኢያሴንዩ እናቱ ደግሞ ቶና ይባላሉ፤ አባትና እናቱ በምግባር አሳደጉት፤ ከዚያም ወደ ገዳም ሄደ በጾምና በጾሎት በብሕትውና (በገዳም) ኖረ፤ እርሱ በነበረበት ዘመን ንጉሥ አክአብና ሚስቱ ኤልዛቤል የተባሉ ነበሩ፤ እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን የማያምኑ በጣዖት የሚያመልኩ ነበሩ፤ ድሮ በኢሎፍላውያን እጅ የነበሩት ጣዖታት (ዳጐንና ቤል) በዚያ ዘመን ወደ እስራኤል ገብተው ነበር። ነብዩ ኤልያስ ግን በዚህ ክፉ ትውልድ መካከል ሆኖም ሥርዓተ ኦሪትን የሚያውቅና እግዚአብሔርን የሚያመልክ ሰው ነበር። በዚያ ወራትም እግዚአብሔር ለነብይነት ጠራው። እርሱም “እሺ” ብሎ ታዝዞ የእግዚአብሔርን የጸጋ ጥሪ ተቀበለ። ነብዩ ኤልያስ ብዙ ጊዜ ለጉዳይ ካልሆነ ከሰው ጋር መዋል ማደርን አይወድምና መኖሪያውን በተራሮችና በዱር አደረገ፤ በተለይ ደብረ ቀርሜሎስ ለእርሱ ቤቱ ነበር። (ድርሳን ነብዩ ኤልያስ የታኅሣሥ ወር)
ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ሕዝቡን እግዚአብሔር ከክፉ ነገር እየጠበቀ፣ የእርሱን ስጦታ እየተመገበ ይኖር ነበር፤ እነርሱ ግን ለቤል (ለበዓል) ለተባለ ጣዖት የሚሰግዱ ነበሩ። ይህን ጊዜ ግን ነብዩ ኤልያስ ወደ አክአብ ዘንድ ሄዶ ጣዖት ማምለክ እንደ ሌለበት ሳይፈራ ገሠጸው፤ (ተቆጣው) ጣዖት የሚያመልክ ከሆነ የሚመጣውን መከራ እንዲህ በማለት ነገረው፦ ‹‹በፊቱ የቆምኩት እስራኤል አምላክ ሕያው እግዚአብሔርን ከአፌ ቃል በቀር በእነዚህ ዓመታት ጠልና ዝናም አይሆንም፤ (፩ኛመጽሐፈ ነገሥት ፲፯፥፩) ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር ዝናም ከሰማይ እንዳይወርድ ተከለከለ። ሕዝቡ በኃጢአቱና ጣዖት በማምለኩ ምክንያት ዝናም ስላልዘነበ እህል በማጣት ተጐዳ። ነብዩ ኤልያስን ግን አምላካችን በዋሻ ተቀምጦ ቁራ የሚበላውን እያመጣለት ይመግበው፣ ምንጭ ፈልቆለት ይጠጣ ነበር።
ከዚያም እግዚአብሔር ሕዝቡ በረኀብ እንደተጎዳ ይመለከት ዘንድ ለነብዩ ኤልያስ ምግብ ይወስድለት የነበረውን ቁራ አስቀረበት፤ ነብዩ ኤልያስም ምግብ ፍለጋ ሰራፕታ ወደ ተባለ ሥፍራ ሄደ፤ በዚያም ነብዩ ባሏ የሞተባትና ዮናስ የተባለ ልጅ የነበራትን ሴት አገኘ፤ እርሷም እንጐቻ ጋግራ ብታበላው ቤቷን በበረከት ሞላው። ታዲያ አንድ ቀን ልጇ ታሞ ሞተባት፤ ነብዩ ኤልያስም በጸሎቱ የሞተውን ልጇን (ሕፃኑ ዮናስን) ከሞትም በጸሎቱ አስነሳላት። (፩ኛነገሥት ፲፯፥፲፯)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ነብዩ ኤልያስ “ለምን ጣዖት ታመልካላችሁ” በማለት ዝናም እንዳይዘንብ ቢያደርግም እግዚአብሔር ለሕዝቡ አዘነ፤ ነብዩ ኤልያስም ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር የዘጋውን ሰማይ ከፍቶት ዝናም እንዲዘንብ አደረገ፤ ሕዝቡንም ሰብስቦ ጣዖት የሚያመልኩም መጥተው መሥዋዕት እንዲሠው አስደረገ፤ ነገር ግን ያመልኩ የነበረው ራሳቸው ሰዎች የሠሩትን ጣዖት ነውና ጣዖቱ ጸሎታቸውን አልሰማቸውም፤ ነብዩ ኤልያስ ግን ገና የእግዚአብሔርን ስም ሲጠራ መሥዋዕቱን ተቀበለለት፤ በዚህም ለሕዝቡ የጣዖታትን ከንቱነት እንዲሁም የእግዚአብሔርን አምላክነት ተረድተው አመኑ፤ ንግሥት ኤልዛቤልም ይህንን ስትሰማ እያልን ልትገድለው ባለች ጊዜ ከፊቷ ፈቀቅ አለ፡፡ (ወደ ሌላ ቦታ ሄደ)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ነብዩ ኤልያስ በዘመኑ ብዙ ድንቅ ነገርን አድርጓል፤ ስለ እውነት ይመሰክር ነበር፤ ለተበደሉ ይከራከር ነበር፤ ለምሳሌ አንድ ጊዜ ኤልዛቤል የተባለችው ንግሥት ናቡቴ የተባለን ሰው አስገድላ መሬቱን ነጠቀችው፤ ነብዩ ኤልያስም ሳይፈራ ወደ ንጉሡ እና ሚስቱ በመሄድ ናቡቴን ገድለው መሬቱን መንጠቅ እንደሌለባቸው በማስገንዘብ ተናገራቸው፤ በዚህም ሊገድሉት አሳደዱት፤ እርሱ ግን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና ሊገድሉት አልቻሉም፤ ነብዩ ኤልያስ ብዙ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ስለ እግዚአብሔር እያስተማረ፣ ሰዎች ከጣዖት አምልኮ እንዲወጡ እየመከረ ከኖረ በኋላ ከዚህ ምድር የሚለይበት ጊዜ ደረሰ፤ የእርሱ ደቀ መዝሙር ለነበረው ነብዩ ኤልሳዕ መጎናጸፊያውን ሰጠው፤ እግዚአብሔርም በእሳት ሠረገላ ጭኖ ወደ ብሔረ ሕያዋን (የቅዱሳን ሰዎች መኖሪያ) ወሰደው፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ነብዩ ኤልያስ ታሪኩ ብዙ ነው፤ በተለይ በመጽሐፍ ቅዱስ በመጽሐፈ ነገሥት ተመዝግቦ ይገኛል፤ እኛ ግን ለግንዛቤ እንዲሆናችሁ ጥቂቱን ታሪክ ነገርናችሁ፤ ብዙ ቁም ነገር እንደምትቀስሙ ተስፋ እናደርጋለን፤ ከነብዩ ኤልያስ ታሪክ የዓለማት ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደሆነ፣ ጣዖት ማምለክ እንደማይገባ፣ እንደ ኤልዛቤል በሰዎች ላይ ክፋት ማድረግ እንደማያስፈልግ፣ እንደ ነብዩ ኤልያስ ስለ እውነት መመስከር እንደሚገባ፣ በእግዚአብሔር መታመን፣ ጾመኛ፣ ጸሎተኛ፣ ለተበደሉና ለተቸገሩ መርዳት እንዳለብን እንማራለን፡፡
ነብዩን ኤልያስን ንጉሥ አክአብና ኤልዛቤል ሊገድሉት ሲሉ እግዚአብሔር ከእነርሱ ከልሎ በዋሻ ውስጥ አስቀምጦ አሞራ ምግቡን እንዲያመጣለት እንዳደረገ ሁሉ እግዚአብሔር ለሚታመኑት፣ ከልብ ለሚከተሉት፣ እውነትን ለሚናገሩና ለሰው ለሚያዝኑ እርሱም እንደሚረዳቸውም ተመልክተናል፤ ስለዚህም በሃይማኖታችን የጸናንና በምግባር የጎለበትን እንሁን! ሥነ ምግባር ያለው፣ ለወላጆች ታዛዥ፣ በሁሉ ነገር ጎበዝና፣ ንቁ ልጆች ልንሆን ያስፈልጋል!
የነብዩ ኤልያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል ታኅሣሥ አንድ ቀን እና ጥር ስድስት ቀን ይከበራል፡።
🙏 አምላካችን እግዚአብሔር ከነብዩ ኤልያስ በረከቱን ያድለን፤ አሜን!
😇 Prophet Elijah (Kidus Elias)
In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC) calendar, the Prophet Elijah (Kidus Elias) is honored, with his birth commemorated on the 1st day of the month of Tahisas (December 10th), a significant feast alongside the birth of the Virgin Mary (Lideta Mariam) and the Archangel Raguel. The EOTC celebrates his miraculous birth, where angels were seen around him, and his life as a great prophet who brought Israel back to God, eventually being taken to heaven in a fiery chariot.
Key Details:
Date: Tahisas 1 (December 10th).
Significance: A monthly feast day celebrating the birth of the Virgin Mary, Archangel Raguel, and Prophet Elijah.
Tradition: Celebrates Elijah's birth in Gilead to righteous parents, with angelic visions at his circumcision, and his life as a lamp to God's people, leading them from idolatry.
Elijah's Role in EOTC Tradition:
Prophet of Fire: Known for his fiery zeal for God and powerful miracles, like bringing rain.
Foregoer of Christ: Believed to be the one who will return before Christ's Second Coming, as prophesied in Malachi.
Ascension: Honored for being taken to heaven alive in a fiery chariot, appearing with Moses at the Transfiguration
According to Ethiopian Orthodox calendar The prophet Elijah was born on December 10 [Tahisas 1], in the province of Gilead, to his righteous parents, his father, Joshua, and his mother, Tonya, who had lived in the house of Levi. On the eighth day, when they had performed circumcision, they named him Elijah.
When the prophet Elijah grew up learning the Law, he left his mother, his father, his relatives, and all his money and lived in the wilderness. St. Paul in the Hebrews' message, "They went about in sackcloth, on carpets, and in goatskins; they were distressed, afflicted, afflicted, hungry, thirsty. These are the things that the world does not deserve: the forest goes for the mountain and the mountain, the cave for the caves and the crumbs for fear. " Hebrews 11:37
"Elijah" also means a lamp to the house of God, that olive oil might shine upon all that are in darkness. When the Israelites were in darkness when they broke into the law of God, worshiping idols, the prophet Elijah arrived and brought them back to God with a bright heart.
One of the great miracles the prophet had done with the power of God was to make rain and to revive again [1 Kings 17: 2]. The sacrifice of the Lord in the presence of the priest, and the disgrace of the priests [2 Kings 18: 38].
One day, as the prophet Elijah was praying, the Angel, the Holy Raguel was revealed and told him, "Rejoice, for the time has come for you to ascend to heaven. You will live in a land of complete happiness. A place where no sickness, death, sorrow, but full of blessing. There is one like you, Enoch, who writes the commandment of the Most High God.
"When the time came for God to bring Elijah to heaven, the prophet went from Gilgal to Jericho, and his disciple Elisha said, "By your living soul, I will not leave you." When they arrived in Jericho, there came small prophets from Jericho. Elijah's ascension was revealed to them by the wisdom of the Holy Spirit, and they said to Elisha, "Do you know that today the Lord will take away your Lord from you?" He said, "I know, keep quiet." Then Elijah went with Elisha, when he said, "Sit down here, for the LORD has sent me to the Jordan . I will not leave you."
Fifty men from the company of the prophets went and stood at a distance, facing the place where Elijah and Elisha had stopped at the Jordan. 8 Elijah took his cloak, rolled it up and struck the water with it. The water divided to the right and to the left, and the two of them crossed over on dry ground.
9 When they had crossed, Elijah said to Elisha, “Tell me, what can I do for you before I am taken from you?” “Let me inherit a double portion of your spirit,” Elisha replied.
10 “You have asked a difficult thing,” Elijah said, “yet if you see me when I am taken from you, it will be yours—otherwise, it will not.”
11 As they were walking along and talking together, suddenly a chariot of fire and horses of fire appeared and separated the two of them, and Elijah went up to heaven in a whirlwind. 12 Elisha saw this and cried out, “My father! My father! The chariots and horsemen of Israel!” And Elisha saw him no more. Then he took hold of his garment and tore it in two. 13 Elisha then picked up Elijah’s cloak that had fallen from him and went back and stood on the bank of the Jordan. 14 He took the cloak that had fallen from Elijah and struck the water with it. “Where now is the Lord, the God of Elijah?” he asked. When he struck the water, it divided to the right and to the left, and he crossed over. [2 Kings 6-14]
As Elijah crossed the Jordan River into the living nations, the believers born of the water and the Holy Spirit will inherit the kingdom of God. Our Lord said in the Gospel of John that "a person who is not born again cannot see the kingdom of God."
The prophet Elijah was one of the fifteen prophets (Moses, Joshua, Samuel, Jonathan, Gad, David, Solomon, Elisha, Ezra, Isaiah, Daniel, Jeremiah, Ezekiel, and John the Baptist). This is a prophet who spoke physically with our Lord on the Mount of Tabor, a priest who broke down the sacrifice of idols, a traditional priest who initiated the ordinance;
Our Lord, our Savior, Eyesus Kirstos, has called John "Elijah" when he witnessed the greatness of the Holy Spirit of baptism. Our Lord calls John “Elijah” because it implies that he is teaching ahead of the Second Coming of Eyesus Kirstos,
James 5:17: "Elias was a man subject to like passions as we are, and he prayed earnestly that it might not rain: and it rained not on the earth by the space of three years and six months."
🙏 May the prayers of Prophet Elijah and St, Raguel the Archangel of JUSTICE be up on us!