Showing posts with label ልደታ. Show all posts
Showing posts with label ልደታ. Show all posts

Saturday, May 9, 2026

WHO’s Dr. Tedros Has a Message About Hantavirus For The People of Tenerife

https://www.bitchute.com/video/X1pCA6rf0mx3/

https://rumble.com/v79mjeo-whos-dr.-tedros-has-a-message-about-hantavirus-for-the-people-of-tenerife.html

🛑 የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ሃላፊ ዶ/ር ቴድሮስ ስለ ሃንታቫይረስ በአስቸኳይ ወደሚጓዙባት ለስፔኗ ቴኔሪፍ ደሴት ህዝብ መልእክት አላቸው፤

በቀጥታ ላናግራችሁ እፈልጋለሁ፣ በፕሬስ መግለጫዎች ወይም በቴክኒካል ገለጻዎች ሳይሆን፣ እንደ አንድ ሰው ለሌላው፣ ምክንያቱም ያንን ይገባችኋልና። …

ቴነሪፌ የተመረጠው የሕክምና አቅም፣ መሠረተ ልማት እና ደህንነትን እንዲያገኙ ለመርዳት የሰው ልጅ ስላለው ነው።

እናም በጥልቅ ስለማምን፣ እኔ ራሴ እዚያ እሆናለሁ። ይህንን ቀዶ ጥገና በአካል ለመመልከት፣ ከጤና ባለሙያዎች፣ ከወደብ ሰራተኞች እና ይህንን እውን ለማድረግ ከሚጥሩ ባለስልጣናት ጎን ለመቆም እና አስቸጋሪ ሁኔታን በጸጋ፣ በአንድነት እና በርህራሄ ምላሽ ለሰጠች ደሴት በግል አክብሮት ለመስጠት ወደ ቴነሪፌ ለመጓዝ አስቤያለሁ። ሰብአዊነትዎ ከሩቅ እውቅና ብቻ ሳይሆን መታየት አለበት።

ብዙ ጊዜ እንደተናገርኩት፡ ቫይረሶች ስለ ፖለቲካ ግድ የላቸውም፣ እና ድንበሮችን አያከብሩም። ማናችንም ያለን ምርጥ መከላከያ አንድነት ነው።

ቴነሪፌ ዛሬ ያንን አንድነት እያሳየች ነው። የመርከቧ ካፒቴን ጃን ዶብሮጎቭስኪ፣ የመርከቧን ሰራተኞች እና የሚያንቀሳቅሰው ኩባንያ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት አርአያነት ያለው ትብብር አሳይተዋል። በዓለም ጤና ድርጅት ስም እና በዓለም ዙሪያ ባሉ ተሳፋሪዎች እና ቤተሰቦቻቸው ስም፣ የቴነሪፌን ህዝብ እና ሌሎችንም ሰዎች አመሰግናለሁ።

እባካችሁ ራሳችሁን እና እርስ በርሳችሁ ተንከባከቡ። በተደረጉት ዝግጅቶች ላይ እምነት ይኑራችሁ። የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከእርስዎ እና በዚያ መርከብ ላይ ካለው እያንዳንዱ ሰው ጋር በእያንዳንዱ እርምጃ እንደሚቆም ይወቁ።

በአክብሮት፣ በእንክብካቤ እና በምስጋና፣

ቴድሮስ"

🧕 አሁን፣ ''ቴነሪፌ/TEnerife + ቴድሮስ/TEdros (The Weeknd) + ቴህራን/TEhran + ቴዎቶኮስ/ THEOTOKOS (ወላዲተ አምላክ ቅድስት ማርያም)'' የሚሉትን ቃል ታች ከአራት ዓመታት በፊት ካቀረብኳቸው ቪዲዮ እና ጽሑፍ ጋር እንጨምርበት።

🚨 ማንም ሰው ባልጠበቀው ቦታ፣ በቴህራን መሃል ላይ 'ቅድስት ማርያም' የሚባል የሜትሮ ጣቢያ አለ። እና በትክክል በኢራን ውስጥ ካሉት ትልቁ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ይገኛል።

በእውነት ድንቅ ነው!

Geneva, May 09, 2026.

“Spain Prepares for Evacuations as Hantavirus Ship Heads for Canary Islands”

To the people of Tenerife:

My name is Tedros, and I serve as the Director-General of the WHO, the UN agency responsible for global public health. It is not common for me to write directly to the people of a single community, but today I feel it is not only appropriate, it is necessary.

I want to speak to you directly, not through press releases or technical briefings, but as one human being to another, because you deserve that.

I know you are worried. I know that when you hear the word “outbreak” and watch a ship sail toward your shores, memories surface that none of us have fully put to rest. The pain of 2020 is still real, and I do not dismiss it for a single moment.

But I need you to hear me clearly: this is not another COVID-19. the current public health risk from hantavirus remains low. My colleagues and I have said this unequivocally, and I will say it again to you now.

The virus aboard the MV Hondius is the Andes strain of hantavirus. It is serious. Three people have lost their lives, and our hearts go out to their families. The risk to you, living your daily life in Tenerife, is low. This is the WHO’s assessment, and we do not make it lightly.

Right now, there are no symptomatic passengers on board. A WHO expert is on that ship. Medical supplies are in place. Spain’s authorities have prepared a careful, step-by-step plan: passengers will be ferried ashore at the industrial port of Granadilla, far from residential areas, in sealed, guarded vehicles, through a completely cordoned-off corridor, and repatriated directly to their home countries. You will not encounter them. Your families will not encounter them.

I also want to say something else, something that goes beyond the science.

I personally thanked Prime Minister Sanchez Castejon for Spain’s decision to receive this ship. I called it an act of solidarity and moral duty. Because that is what it is. I want you to know that the WHO’s request to Spain was not made arbitrarily. It was made in full accordance with the International Health Regulations, the legally binding framework that defines the rights and obligations of countries and the WHO when responding to public health events of international concern. Under those rules, the nearest port with sufficient medical capacity must be identified to ensure the safety and dignity of those on board. Tenerife met that standard. Spain honoured it. Nearly 150 people from 23 countries have been at sea for weeks, some of them grieving, all of them frightened, all of them longing for home. Tenerife has been chosen because it has the medical capacity, the infrastructure, and the humanity to help them reach safety.

And because I believe that so deeply, I will be there myself. I intend to travel to Tenerife to observe this operation firsthand, to stand alongside the health workers, port staff, and officials who are making it happen, and to personally pay my respects to an island that has responded to a difficult situation with grace, solidarity, and compassion. Your humanity deserves to be witnessed, not just acknowledged from a distance.

As I have said many times: viruses do not care about politics, and they do not respect borders. The best immunity any of us has is solidarity.

Tenerife is demonstrating that solidarity today. The ship’s captain, Jan Dobrogowski, crew and the company operating the vessel have shown exemplary collaboration at this challenging time. On behalf of the World Health Organization, and on behalf of those passengers and their families around the world, I thank the people of Tenerife and everyone else involved.

Please take care of yourselves and of each other. Trust in the preparations that have been made. And know that the WHO stands with you, and with every person on that ship, every step of the way.

With respect, care, and gratitude,

Tedros

🧕 Now, let's add, ''TEnerife + TEdros (The Weeknd) + TEhran + THEOTOKOS (Mary The Mother of God) to the video and text below:

🛑 Texas Orders Unauthorized Dallas-Area Muslim ‘University’ to Cease Operations Immediately

🛑 Texas & Tegray (Ethiopia) Massacres + Tedros (TE) & The Queen | ትግራይና ቴክሳስ + ቴድሮስ & ንግሥቲቱ

https://www.bitchute.com/video/g5mCQ8yM2u4I/

🚨 In the heart of TEhran, somewhere nobody expected, there is a metro station called 'Holy Mary'. And it's located exactly in front of the biggest church in Iran.

🧕 The Birth of The Virgin Mary, Lideta LeMariam | ልደታ ለማርያም

https://axumitethiopia.blogspot.com/2026/05/the-birth-of-virgin-mary-lideta-lemariam.html

https://www.bitchute.com/video/FuLGkBw3TgN7/

https://rumble.com/v79m9mk-the-birth-of-the-virgin-mary-lideta-lemariam-.html


😇 ዛሬ ቅዳሜ ፲፬ ነሐሴ ፳፻፲፬ ዓ.ም የአባታችን የአቡነ አረጋዊ ዕለት ነው።

🛑 ክቡራን እና ክቡራት፤ እምላለሁ; አሜሪካ የኢትዮጵያን እኩይ ፋሽስት ኦሮሞ መንግስት መደገፏን ካላቆመች ፥ ብላም ታሪካዊቷን የክርስቲያን-ጽዮናዊት ኢትዮጵያን ለመበታተን፣ ለማዳከም እና ለማፍረስ ከያዘችው ዲያብሎሳዊ ሴራ ካልተቆጠበች፣ ምናለ በሉኝ፤ በቅርቡ የቴክሳስ ግዛት ከዩናይትድ ስቴትስ ብሄራዊ ሕብረት የምትገነጠል የመጀመርያዋ ግዛት ግዛት ትሆናለች።

ቴክሳስ

ትግራይ

ቴዎድሮስ

ቴስላ (የቴስላ የምርት ስም ባለቤት በተጨማሪም ኤሎን ማስክ የኢቴሬም /Ethereum ምናባዊ/ምስጢራዊ ምንዛሬ ባለቤት ነው CRYPTO: ETH = ኢትዮጵያ)

👉 የኤሎን ማስክ እርባታ/ መኖሪያ ቤት እና የእሱ 'ስፔስ ኤክስ' 'ስታር ቤዝ' የጠፈር ጣቢያ በቴክሳስ ይገኛሉ።

😇 Today, according to the Ethiopian calendar it's Saturday, August 14, 2014 – Saint Abuna Aregawi commemorated on this very Day.

💭 Ladies and gentlemen; I swear to you; If America does not stop supporting the evil fascist Oromo regime of Ethiopia – and if it does not refrain from its diabolical plot to disintegrate, weaken and destroy the historical Christian-Zionist Ethiopia – then, mark my words, the state of Texas would become the first state to secede from the National Union of the United States of America very soon.

TExas

TEgray (Tigray)

TEdros (Tigray Native)

TEsla (Besides, Elon Musk owns Ethereum (CRYPTO: ETH = Ethiopia)

👉 Elon Musk's ranch and his SpaceX Starbase are located in Texas.

https://www.dailymail.co.uk/news/article-10775779/Elon-Musks-50k-Texas-home-near-SpaceX-Starbase-revealed.html

The Birth of The Virgin Mary, Lideta LeMariam | ልደታ ለማርያም

https://www.bitchute.com/video/FuLGkBw3TgN7/

https://rumble.com/v79m9mk-the-birth-of-the-virgin-mary-lideta-lemariam-.html

♰ The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church celebrates the birth of the Virgin Mary, known as Lideta LeMariam (or Lideta), on Ginbot 1 (May 9 in the Gregorian calendar).

The feast commemorates her birth to Joachim and Anna—a birth believed to have marked the end of darkness and the beginning of salvation.

Key Aspects of the Celebration and Belief:

🧕 Significance: Mary's Birth is seen as the "star of the dawn" that heralded the coming of Jesus Christ, the Sun of Justice.

Parents: According to tradition, her parents, Joachim and Anna, were righteous but elderly and barren. They fasted and prayed for a child, promising to dedicate them to God, resulting in the birth of Mary.

Immaculate Conception: Ethiopian tradition considers Mary to be pure and holy from her conception, as she was born to bring forth the Incarnated Word, often viewed as being preserved from the original sin of Adam.

Celebration: The festival involves solemn church services, singing of "Lideta leMariam" hymns, and sometimes fasting beforehand. The birth is also commemorated on the 1st of every month in the Ethiopian calendar.

Location: While major celebrations happen throughout Ethiopia, Lalibela is a particularly significant site for this holiday.The Ethiopian Orthodox Church celebrates the Immaculate Conception of St. Mary by her mother Anna on Nehasie 7 (August 13), exactly nine months before her birth on Ginbot / May.

🧕 ከቅዱሳን ውስጥም ፍጥረት ሁሉ በንጽህና የማይተካከላት የብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት

😇 ከቅዱሳን ውስጥም ፍጥረት ሁሉ በንጽህና የማይተካከላት የብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷን ታሪክ ምእመናን ዘወትር ወር በገባ በመጀመሪያው ቀን "ልደታ" ብለው በመሰየም፣ በግንቦት ፩ ከዋዜማ አንስቶ በእለቱ በደማቅ ሥርዓት ከውጭ በመሆን ያከብሩታል፡፡ በዚህ ብቻ ሳይወሰኑ በሊባኖስ ተራራ የተፈጸመውን ድንቅ ተአምር በዝማሬ ያስቡታል፡፡ ከዝማሬ በተጨማሪም ሥዕሏን በመሣል እና አጠገባቸው አድርገው በመማጸን የእመቤታችን ልደትን ያከብራሉ፡፡

ቅዱሳት ሥዕላት ደግሞ የቅዱሳንን የሕይወት ጉዞና ተጋድሎ ፍንትው አድርገው በማሳየት ከቅዱሳን ጋር ኅብረት አንዲኖረን ያደርጋሉ፡፡ እኛም ከሁለት ሺ ዓመታት በፊት በሊባኖስ ተራራ የተፈጸመውን ታላቅ ተአምር በሥዕሉ አማካኝነት የደስታው ተካፋይ እንሆናለን፡፡ በመሆኑም የእመቤታችን ልደት ስናስብ ልቦናችን በተመስጦ ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሔድ እና መልካም ልደት እንድንላት ለውዷ እናታችን ከሥር ትውፊታቸውን የጠበቁ ሥዕሎች ቀርበዋል፡፡ በተጨማሪም በሥዕሏ ላይ የሚታዩ ዐብይት ጭብጦች በአጭሩ ተዘርዝረዋል፡፡

የእመቤታችን ልደታ ሥዕል በቤተ ክርስቲያን ሲሣል የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች ታሪክን በሚያጎላ መልኩ ይሣላል፡፡ ለምሳሌ ልጅ ባለመውለዳቸው ምክንያት አዝነው፣ ተኝተው ራእይ ሲመለከቱ እና እመቤታችን ተወልዳ ቅደስት ሐና አቅፋት ኢያቄም ደግሞ ሲመለከት ለብቻቸው ሆነው አሊያም ሌሎች ሰዎች የቅዱሳኑን ደስታ ለመካፈል በአካል መገኘታቸውን በሥዕል ይገለጣል፡፡

ከሥርም እነዚህን ታሪኮች የሚያብራሩ የብራና የግድግዳ እና የገበታ ጥንታዊ ሥዕሎች ቀርቧል፡፡ መልካም በዓል፡፡ እመቤታችን ከዚህ መቅሰፍት ትሰውረን ለቀጣይ ዐመትም በደስታ ከቁጥር ሳንጎደል "ልደትሽ ልደታችን ነው" ብለን አንድናመሰግናት እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

🧕 ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት | ምስጋና

❖❖❖ ልደታ ለማርያም፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ❖❖❖

❖❖❖በሰንበት ተማሪዎች የቀረበ ወረብ❖❖❖

የቅድስት ልደታ ለማርያም ክብረ በዓል ፩ ግንቦት ፪ሺ፱ ዓ.

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም "የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት" ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ “ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች” [ኢሳ ፯፡፲፬] ብሎ ትንቢት የተናገረላት ያቺ ድንግል በዚህች ዕለት ተወለደች፡፡ ይህች ቀን ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት " የወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።” [መዝ ፵፬፡፱] ብሎ የተናገረላት ንግሥት የተገኘችባት ዕለት ናት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ “ፀሐይን የተጎናጸፈች፣ ጨረቃን የተጫማች፣ አስራ ሁለት የክዋክብት አክሊል በራሷ ላይ ያላት።”[ራዕ ፲፪፡፩] ብሎ የመሰከረላት የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችባት ቀን ናት፡፡ የእርስዋም ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራዕይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን ሲገለጽ የነበረ ነው፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በነቢያት አንደበት

መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡ መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ [መዝ ፹፮፥፩፡፯]

እግዚአብሔር የዝማሬና የትንቢት ጸጋን ያበዛለት ክቡር ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥርወ ልደት አስቀድሞ በመንፈስ ቅዱስ መነጽርነት ተገልጾለት "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን /መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው/" በማለት ትንቢት ተናግሯል፡፡ "የተቀደሱ ተራሮች" ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ይህንን ትንቢትና እውነተኛውን የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ ቤተክርስቲያን "የእመቤታችን ማርያም ትውልዷ ባባቷ በኩል ከንጉሡ ከዳዊት ወገን ነው፤ በናቷም በኩል ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው፤ የአባቷ ስም ኢያቄም ነው፤ የእናቷም ስም ሐና ነው፡፡" ብላ ታስተምራለች፡፡

ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡ [ኢሳ. ፲፩፡፩]

ቁጥሩ ከዐበይት ነቢያት ወገን የሆነው ነብዩ ኢሳይያስም ጥበብንና እውቀትን በሚገልጽ ስለሚመጣውም ነገር ትንቢትን በሚያናግር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም ጽጌ (አበባ) የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት "ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ /ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል/" በማለት ታላቅ ትንቢትን ተናግሮ ነበር፡፡ ይህች በትርም ከእሴይ ዘር የተገኘችው በዚህች ዕለት ነውና ልደቷን በታላቅ ድምቀት እናከብራለን፡፡ ይህንን መሰረት በማድረግ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም "መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከእሴይ ሥር የተገኘሽ መዓዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ" በማለት በውዳሴ አመስግኗታል፡፡ "በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ” [መዝ.፻፴፩፡፲፫]" የተባለልን የአባቶቻችን ልጆች እኛም እንዲሁ እያልን እናመሰግናታለን፡፡

ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ፡ ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ፡፡ [መኃ ፬፡፰]

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ በሊባኖስ ስለመሆኑ አስቀድሞ ጠቢቡ ሰሎሞን "ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ ንዒ ወተወፅኢ እምቅድመ ሃይማኖት እምርእሰ ሳኔር ወኤርሞን አምግበበ አናብስት ወእምአድባረ አናምርት /ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔር ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች/" በማለት ተናግሮ ነበር፡፡ የዚህ ትንቢት ምስጢርም የእመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸው የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ ትንቢቱም ሲፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት ፩ ቀን በ፲፭ ዓ.ዓ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች፡፡

ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ የተባለው የነገረ ማርያም ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እመቤታችን በሊባኖስ እንደምትወለድ አስቀድሞ ሰሎሞን የተናገረው ቃልም መፈጸሙን ሲገልጽ "….የአናብስት ልጅ አልኩሽ፡፡ ሰሎሞን እንዲህ ሲል እንደተናገረ፡- ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሽ ነዪ፤ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው፡፡" በማለት አመስጥሮታል፡፡ እመቤታችንም በሊባኖስ ተራራ እንድትወለድ ምክንያት የሆነው በማሕፀን ሳለች የአርሳባንን ልጅ ዓይን በማብራቷና ሳሚናስ የሚባለውን የጦሊቅን ልጅ ከሞት በማስነሳቷ አይሁድ በቅናት ተነሳስተውባቸው ስለነበር ሐናና ኢያቄም ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሄዱ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ስለነገራቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌ

ከትንቢቱ በተጨማሪም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌም አስቀድሞ የተገለጸ ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል ከእርሷ ሰባት ትውልድ አስቀድሞ ለነበሩት ደጋግ ሰዎች እንዲሁም ለእናትና ለአባቷ የተገለጹት ምሳሌዎች በቅዱሳት መጻሕፍት በሰፊው ሰፍረው ይገኛሉ፡፡

ሰባተኛዪቱ እንቦሳ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋ ደግሞ ፀሓይን ስትወልድ አየሁ (ቴክታ)

በቅድስና የሚኖሩ ነገር ግን መካን የነበሩት ቴክታና ጴጥርቃ ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ ፤ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ስድስት ስትደርስ ፤ ስድስተኛዪቱ ጨረቃን ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሀገራቸው መፈክረ ሕልም (ሕልም ፈች ሊቅ) አለና ሂደው ነገሩት፡፡ ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ፤ ጨረቃይቱ ከፍጡራን በላይ የምትሆን ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡ የፀሐይ ነገር ግን አልተገለጸልኝም፤ እንደ ነብይ እንደ ንጉሥ ያለ ይሆናል አላቸው፡፡ እነርሱም ጊዜ ይተርጉመው ብለውት ሄዱ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጅ ወለዱ፡፡ ስሟንም "ረከብኩ ስእለትዬ፤ ረከብኩ ተምኔትዬ" /የተሳልኩትን አገኘሁ፤ የተመኘሁትን አገኘሁ/ ሲሉ "ሄኤሜን"አሏት፡፡ ሄኤሜን ዴርዴን፤ ዴርዴ ቶናን፤ ቶና ሲካርን፤ ሲካር ሄርሜላን፤ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡ ሐና ለአካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ ይሑዳ ለተወለደ ኢያቄም ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት፡፡ ከኢያቄምና ከሐናም በጨረቃ የተመሰለች ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡

ፀዓዳ ርግብ ሰባቱ ሰማያትን ሰንጥቃ መጥታ በማሕፀኔ ስታድር አየሁ (ቅድስት ሐና)

ኢያቄምና ሐና መካን ስለነበሩ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ጸልየው፤ ሲሰጣቸውም መልሰው ለእርሱ እንደሚሰጡ ስዕለትን ተስለው ነበር፡፡ ጸሎታቸው ሲደርስ ለሐና በሕልም ተገልጾላት ለባለቤቷ ለኢያቄም "ብእሴሃ አነኑ ርኢኩ በሕልምየ ርግብ ጸዐዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርእስየ ወቦአት ውስተ እዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርሥየ /ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብቶ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ፡፡" ብላዋለች፡፡ የዚህ ራእይ ምስጢርም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን፤ ፀዓዳ (ነጭ) መሆኗ ንጽሕናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ዘላለማዊ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ" ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን የምትፀንሰውን ንጽሕት ርግብ የተባለችውን እመቤታችንን የምትወልድ መሆኗን ሲያጠይቅ ነው።

ከሰባተኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ (ቅዱስ ኢያቄም)

በተመሳሳይ ኢያቄምም በሕልሙ ያየውን ለባለቤቱ ለሐና "እንዘ ይትረኀዉ ሰብዐቱ ሰማያት ዖፍ ጸዐዳ መጽአ ኀቤየ ወነበረ ዲበ ርእስየ /ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ" ብሎ በሕልሙ የተገለጸለትን ነግሯታል፡፡ የዚህም ራዕይ ምስጢር ዖፍ የተባለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባሕርዩ ነው፡፡ ኢያቄም "ከላይ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ" ማለቱ የኢያቄምን ባሕርይ ባሕርይ እንደሚያደርግ የሚያጠይቅ ሲሆን ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ባህርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩና መንግስቱ ናቸው።

የድንግል ማርያም ልደት በሐዲስ ኪዳን ሊቃውንት

የሐዲስ ኪዳን ሊቃውንትም ትንቢተ ነቢያትንና ወንጌልን በማጣጣም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት አመስጥረው አስተምረዋል፤ አመስግነዋል፤ ተቃኝተዋልም፡፡ የእርሷን ልደት እጅግ ብዙ ሊቃውንት በስፋትና በጥልቀት ያመሰጠሩት ሲሆን ለምሳሌ ያህል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡

ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች (ቅዱስ ያሬድ)

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ልደት "ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ/ ማርያምስ (ማርያም ግን) ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች፡፡" በማለት እርሷ በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና፣ በቅድስናና በድንግልና ስታበራ እንደነበርና ኋላም የዓለም ብርሃን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መውለዷን አመስጥሮ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም ስለ ሥርወ ልደቷ "እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕጹቂሃ…ሐረገ ወይን/ ሥሮቿ በምድር ጫፎቿም በሰማይ ያሉ…የወይን ሐረግ" በማለት የተወለደችው በምድር ከነበሩት ኢያቄምና ሐና መሆኑን የወለደችው ግን ሰማያዊውን ንጉሥ እንደሆነ በማመስጠር ዘምሯል፡፡ በዚህም ሰውና እግዚአብሔርን ያገናኘች መሰላል መሆኗል ገልጾ አስተምሯል፡፡

ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ (አባ ሕርያቆስ)

የብህንሳው ሊቀ ጳጳስ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም "ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ/ ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ" በማለት የድንግል ማርያም ጽንሰትና ልደት እንዴት እንደነበር በድርሰቱ አስፍሮታል፡፡ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚላት የሁላችን እናት ድንግል ማርያም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኋላ ግንቦት ፩ ቀን ተወልዳለች፡፡ እርስዋም ስትፀነስ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ከጥንተ አብሶ (original Sin) ጠብቋታል፤ አበሳው አልነካትም፡፡ ይህንንም ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በኃጢአት በተከበበ፣ መርገም በሞላበት ዓለም ውስጥ ከኃጢአት ከበደል ርቃ (ተለይታ) እንደ ጌዲዮን ጸምር በንጽህና የጠገኘች ንጽህት ዘር መሆኗን ሲያስረዳ "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር፡፡"[ኢሳ.፩፡፲፱]በማለት ተናግሯል፡፡ እንዲሁም ጠቢቡ ሰሎሞን ንጽህናዋን በትንቢት መነጽር አይቶ “ወዳጄ ሆይ፣ ሁለንተናሽ ውብ ነው፣ ምንም ነውር የለብሽም፡፡ ሙሽሪት ሆይ ከሊባኖስ ነዪ፡፡”[መሓልይ ፬፡፯፡፲፮] በማለት በንጽህና በቅድስና ያጌጠች፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያልነካት፣ የድህነታችን ምክንያት፣ የንጽህናችን መሰረት የሰው ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲዋሀድ ምክንያት የሆነች ንጽሕት የሰርግ ቤት ድንግል ማርያም በሊባኖስ የመወለዷን ነገር አስቀድሞ ነግሮናል፡፡

ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት (ቅዱስ እንድርያስ)

የቀርጤሱ ቅዱስ እንድርያስ የከበረ ስለሆነው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ታላቅነት "ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌው በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል፤ የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ ዕለት (ጌታ) መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነው፡፡” በማለት ገልጾታል፡፡ በእውነት የእርሷ ልደት የልዑል ማደሪያው መቅደስ የተሰራበት ዕለት ነውና ሁላችን እናከብረዋለን፡፡ በዚህም ዕለት "ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም/ እነሆ ዛሬ በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ" እያልን እንዘምራለን። ይህችን የልዑል ማደሪያ እናቷ ሐናና አባቷ ኢያቄምም በእጅጉ ተደስተው በተወለደች በስምንተኛ ቀኗ ስሟን "ማርያም" ብለው ሰይመዋታል፡፡

የእመቤታችን የልደት በዓል አከባበር

አባታችን አዳም በኃጢአት ከወደቀ በኋላ፣ ንስሃ በገባ ጊዜ አምላካችን ጌታ እግዚአብሔር የድህነት ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ቃል ኪዳኑም “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚል ነበር፡፡ ስለሆነም አዳም ፶፻፭፻/5500 ዘመን የሕይወት ምክንያት የሆነች የልጅ ልጁ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአብራኩ ከተከፈሉ ቅዱሳን ልጆቹ የምትወለድበትን ቀን ተስፋ እያደረገ ኖረ፡፡ የእመቤታችንን የድንግል ማርያምን የመወለዷን ዜና ተስፋ በማድረግ “ሴት” ይላት የነበረውን ሚስቱን ሔዋንን በእመቤታችን ምሳሌነት “ሔዋን”፣ የሕያዋን ሁሉ እናት ብሎ ሰየማት፡፡ [ዘፍ.፫፡፳] ዳግማዊ አዳም የተባለ ክርስቶስም የአዳምን ተስፋ በመስቀል ላይ በፈጸመ ጊዜ እውነተኛዋን ሔዋን (ዳግሚት፣ አማናዊት ሔዋንን) ድንግል ማርያምን በዮሐንስ ወንጌላዊ በኩል ለሕያዋን ምዕመናን ሁሉ እናት አድርጎ ሰጠ፡፡ [ዮሐ. ፲፱፡፳፮] ይህን የከበረ ምስጢር የማይረዳ “ክርስቲያን” እንዴት ያሳዝናል!? እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን የቀዳማዊ አባታችንን የአዳምን፣ እንዲሁም በዳግም ተፈጥሮ ያከበረንን ዳግማዊ አዳም የተባለ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ተቀብለን “የሕያዋን ሁሉ እናት” ድንግል ማርያምን ልደቷን በፍፁም ደስታ እናከብራለን፣ ከተወደደ ልጇ ምሕረትን ትለምንልን ዘንድም ወደ እርሷ እናንጋጥጣለን፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያለን ምዕመናን ከጌታችን ልደት ቀጥሎ በታላቅ ድምቀት የምናከብረው የልደት በዓል የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ነው፡፡ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ "በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።"[ሉቃ ፩፡፲፬] ከተባለ የድንግል ማርያም ልደት ምንኛ የሚያስደስት ይሆን?! የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት፣ የታየው ራዕይም በገሀድ የተከናወነበት፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ (ለሕያዋን ሁሉ) ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም በንጽህናዋ በቅድስናዋ ተደንቀው “እህትነ ነያ/እህታችን እነኋት” ብለው ያመሰግኗታል፡፡ በዘመናችን ያሉ የሰዎች ልደት በድምቀት የሚከበር ከሆነ ለሰው ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ምንኛ ሊከበር ይገባው ይሆን?! ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡ የሕይወት ክርስቶስ እናት ዛሬ ተወልዳለችና፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትዉፊት መሰረት ሐና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ፡፡ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ "ንፍሮና ጥራጥሬ" ነበር፡፡ይህንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ነገር ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መካከል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳዊ በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ (የእመቤታችን የልደት በዓል) ነዉ፡፡ በዚህ ዕለት አንዳንዶች ባለማወቅ ሌሎች ደግሞ በድፍረት "ለአድባር አዉጋር ነዉ፤ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ" እያሉ ለማያውቁት አምልኮ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቅቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ አሉ፡፡ እውነታው እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን እነዚህን የሃይማኖት ለዋጮች ሥራቸውን እንጸየፋለን፡፡ ስለሆነም ከእንደዚህ ዓይነቱ ባዕድ አምልኮ በመለየት ይህንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር ልናከብረው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ በምሕረቱ የጎበኘንን አምላካችንን ብቻ እያመለክን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን፡፡

WHO’s Dr. Tedros Has a Message About Hantavirus For The People of Tenerife

https://www.bitchute.com/video/X1pCA6rf0mx3/ https://rumble.com/v79mjeo-whos-dr.-tedros-has-a-message-about-hantavirus-for-the-people-of-t...