Showing posts with label ጽዮን. Show all posts
Showing posts with label ጽዮን. Show all posts

Friday, April 10, 2026

✞ Crucifixion | On That Day, Children of Christ Became Christians & Children of the Antichrist Muslims

https://www.bitchute.com/video/5lkPo8oIrLVD/

https://rumble.com/v6s8bp9-crucifixion-on-that-day-children-of-christ-became-christians-and-children-o.html

የጌታችን ስቅለት | በዚያን ዕለት የከርስቶስ ልጆች ክርስቲያን፤ የክርስቶስ ተቃዋሚው ልጆች እስላም ተባሉ

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ "የድኅነት ቀን" ይባላል፡

፲፫ቱ ሕማማተ መስቀል

  • ፩ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)

  • ፪ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)

  • ፫ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይ መውደቅ)

  • ፬ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድ መረገጥ)

  • ፭ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋር መላተም)

  • ፮ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)

  • ፯ኛ. ተቀስፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)

  • ፰ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)

  • ፱ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)

  • ፲ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)

  • ፲፩ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)

  • ፲፪ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይ መሰቀል)

  • ፲፫ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትን መጠጣት)

ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤

  • . ፀሐይ ጨለመ፤

  • . ጨረቃ ደም ኾነ፤

  • . ከዋክብት ረገፉ፤

  • . የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤

  • . አለቶች ተፈረካከሱ፤

  • . መቃብራት ተከፈቱ፤

  • . ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩-፶፬)፡፡

ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል፤

  • . "ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)"

  • . "እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ"

  • . "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው"

  • . እመቤታችንን "ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ" ደቀ መዝሙሩንም "እናትህ እነኋት" በማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤

  • . "አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ"

  • . "ተጠማሁ"

  • . "ዅሉ ተፈጸመ" (ማቴ. ፳፯፥፵፭-፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫-፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲-)፡፡

ከሰድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጨለማ ኾኖ ከቈየ በኋላ ከዘጠኝ እስከ ማታ እንደ ተለመደው ብርሃን ሁኖአል፡፡ "ወፍና ሠርክ ይበርህ ብርሃነ ፀሐይ" እንዲል (ዘካ. ፲፬፥፯)፡፡ በዚህ ዕለት ሰባት መስተፃርራን (ጠበኞች) ታረቁ፤ ተስማሙ፡፡ እነዚህም፡- ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው (ኤፌ. ፪፥፲፤ ቈላ. ፩፥፳)፡፡ ጌታችን ጠዋት በሦስት ሰዓት ተገረፈ፤ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ (ማቴ. ፳፯፥፩-፴፯፤ ሉቃ. ፳፫፥፩-፵፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፩)፡፡

ጌታችን በውኃው ተጠምቀን፣ ደሙን ተቀብለን የእግዚአብሔር ልጆች እንኾን ዘንድ ከቀኝ ጎድኑ ጥሩ ውኃ፣ ትኩስ ደም አፈሰሰልን (ዮሐ. ፲፱፥፴፬)፡፡ በዐሥራ አንድ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው ሽቶ እየረበረቡ በድርብ በፍታ ገንዘው ቀበሩት (ሉቃ. ፳፫፥፶-፶፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፴፰-፵፪)፡፡ ነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዳ ነፍሳትን ነጻ አወጣች (፩ኛ ጴጥ. ፫፥፲፱)፡፡ በዚህ ጊዜ በርሃነ መለኮቱ በሲኦል ተገለጠ፡፡ ስለዚህም "ንሴብሖ ለእግዚአብሔር" እየተባለ ይዘመራል፡፡ ከሆሣዕና አንሥቶ ተከልክሎ የነበረው ኑዛዜ ይናዘዛል፤ ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፡፡

ጌታም ቆላተ ዮሳፍጭ ከሚባል በረሀ አውርዶ መናውን ውሀውን ከወትሮ አብልጦ አወረደላቸውና ኃይሉን ከሂሎቱን አሳይቶ ወእንዘ ዓዲ መብልዖሙ ውስተ አፋሆሙ ነዘር እባብ አስንቶ ጐዳናቸውን እየስቀደደ አስፈጃቸው። ሙሴም አቤቱ ጌታዬ አሕዛብ ፳ኤልን የሚመግባቸው ቢያጣ ከበረሀ አውርዶ አስፈጃቸው እንዳይሉህ መድኃኒት ፈልግላቸው ብሎ ጸለየ። ጌታም የወዳጁን ጸሎት ፈጥኖ ይሰማልና ብርቱን እባብ አስመስለህ በተራራ ላይ ተራዳ ተክለህ ብርቱን በዚያ ላይ ሰቅለህ አሳያቸው ያን አይቶ ሰምቶ ያመነ ይዳን ያላመነ ይፈጸም አለው። ተራራው በቀራንዮ አምሳል ነው፤ ተራዳው የመስቀል ብርቱ የወልደ እግዚአብሔር እባብ የዲያብሎስ ቍስሉ የኃጢአት መርዙ የመርገመ ሥጋ የመርገመ ነፍስ በረኃው የገሃነም እሳት አምሳል ነው።

ያን አይተው ሰምተው ይዳኑ ማለት ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያመኑ ሐዋርያት፣ ሰምተው ያመኑ ምዕመናን የመዳናቸው አምሳል ነው። ያላመኑ ይፈጸሙ ማለቱ፡ ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያላመኑ አይሁድ ሰምተው ያላመኑ አይሁድ፣ ሰምተው ያላመኑ አሕዛብ ያለመዳናቸው አምሳል ነው።

ነፍስ ያለው እባብ የገደላቸውን ሰዎች ነፍስ የሌለው ብርት እንዳዳናቸው በባሕርዩ ሞት የሌለበት አምላክ ዲያብሎስ ያስገራቸውን ነፍሳት ተሰቅሎ ሞቶ የማዳኑ አምሳል ነው።

ጽዮን የተባለች ማኅፀነ ማርያም ደብረ መቅደሱ የተባለ አካሏ ነው

ጌታም እነዚያ አላወቁም እንጂ እኔስ በማኅፀነ ማርያም አድሬ ለጻድቃን ለሰማዕታት ነገሥሁላቸው በአይሁድ በመናፍቃን ነገሥሁባቸው ሲል ነው። አንድም ጽዮን የተባለ መሰቀሉ ደብረ መቅደሱ የተባለ አካሉ ነው

እነዚያ አላወቁም እንጂ እኔስ በመስቀል ተሰቅዬ ለጻድቃን ለሰማዕታት ነገሥሁላቸው በአይሁድ

በመናፍቃን ነገሥሁባቸው ሲል ነው እንዲህ ፯ት ተአምራት ሲሠሩ አይተው የባሕርይ አምላክ ነው እንጂ የባሕርይ አምላክማ ካልሆነ እንዲህ ያሉ ተአምራት ባልተሠሩ ነበር ያሉ ክርስቲያን ተባሉ።

አምላክ አይደለም፣ አልተወለደም፣ አልተሰቀለም፤ የአምላክ ወዳጅ ደግ ሰው ነብይ ብቻ እንጂ ያሉት እስላም ተባሉ። እስላምና ክርስቲያን የተባለበት ያን ዕለት ነው።

አይሁድ ግን አላክም ነብይም አይደለም ሐሳዌ መሲሕ ነው ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለም ብለው ካዱት።

መናፍቃን ካህናት አላውያን መኳንንት ከሀድያን ነገሥታት ሃይማኖታችሁን ጣሉ ፈጣሪያችሁን ካዱ ለጣኦት ስገዱ ብለው እንደ እኔ እራሳችሁን እየመቱ አክሊለ ሦክ ግንድ አሸክመው በብረት ቢቸነክሯችሁ መራር ሐሞት ቢያጠጧችሁ ዋጋችሁን በመንግሥት ተቀበሉት እንጂ ሃይማኖታችሁን አትጣሉ፤ ፈጣሪያችሁን አትካዱ፤ ለጣኦት አትስገዱ!በማለት ጌታችን አስተምሮናል።

ከፍኖተ መስቀሉ ከህያው ቅዱስ ቃሉ በረከት ይክፈለን

✞ Today millions of Orthodox Christians commemorate Good Friday, also known as “Great Friday” to remember the events leading up to Jesus' Crucifixion.

In Ethiopia, Good Friday is known locally as Siklet which translates to Crucifixion of the Lord Jesus Christ. It is a day of fasting, intense prayer and prostrations.

Followers of Ethiopian Orthodox Churches share the religious tradition with other Orthodox Churches. In Ethiopia, churches outside the Ethiopian Orthodox Church including Catholic celebrate the good Friday along with the Ethiopian Church.

Good Friday is the holiday that Lord and Savior Jesus Christ was crucified for the salvation of human race. He was beaten hard, spited on and dragged with a robe all the way through to Calvary.

After His capture betrayed by Judas on Thursday eve subsequent to His prayer in Gethsemane, the Jews took Him and started their torture. Early morning on this Holy Friday, Lord Jesus Christ was brought to trial in front of the Jewish leader Pilate. Convicted for a crime He did not commit, Lord Jesus was tortured and tormented until He reached to the Calvary for crucifixion. Upon it was revealed miracles including the darkening of the sun, the bleeding of the moon and the falling of the stars whilst Lord Jesus Christ separated His divine soul from His body at the ninth hour. Then after, Joseph and Nicodimus took His holy body and buried it.

✞ A chapter in one of the Prayer books (The Passion of Cross or Himamat Meskel) of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church teaches us the following very important lesson:

“They did not know, but I was crucified and reigned over the righteous and the martyrs, so the Jews who saw those 7 miracles being done, were called Christians because they said that it could only be a God of nature who is showing us these miracles, and if He was not a God of nature, such miracles would not have been done.„

And,

☪ “Those who deny the divinity of Jesus by saying, „He is not God, He was not born, He is not The Son of God, God doesn't have a son, He was not crucified, He is only a friend of God, a good man and just a prophet; They are called Muslims, or followers of Islam. It was on that very day that Islam and Christianity were called as such.”

May God accept our prayer, fasting and all our endeavors on the great lent and redeem us; Amen!

The Good Friday procession of the Ethiopian Orthodox Church in Jerusalem | ስቅለት በኢየሩሳሌም

https://www.bitchute.com/video/HwTCCb7lHHqN/

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

ስቅለት ዕለተ ዓርብ በአክሱም ጽዮን፤ ሕፃናቱ፤ “ኪራላይሶን/አቤቱ ይቅር በለን ማረን!” ሲሉ፤ እንባዬ ዱብ ዱብ አለ!

💭 ከሦስት ዓመታት በኋላ ነው ይህን ስናይ!

[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፶፲፬፲፯]❖

ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት ሠዋ፥ ለልዑልም ስእለትህን ስጥ፤ በመከራ ቀን ጥራኝ፥ አድንህማለሁ አንተም ታከብረኛለህ።

ኃጢአተኛውን ግን እግዚአብሔር አለው። ለምን አንተ ሕጌን ትናገራለህ? ኪዳኔንም በአፍህ ለምን ትወስዳለህ? አንተስ ተግሣጼን ጠላህ፥ ቃሎቼንም ወደ ኋላህ ጣልህ።”

😇 እግዚአብሔር አምላካችን፣ ቅድስት እናቱ ጽዮን ማርያም እና ቅዱሳኑ ከእናንተ ከአክሱም ጽዮናውያን ጋር ናቸው ዛሬ፤ ነፍሶቼ! ሕፃናቱ፣ ሕፃናቱ፣ ሕፃናቱ። 😢😢😢

ያን ሁሉ ግፍ፣ መካራና ስቃይ እያሳላፈችሁ አምላካችሁ፣ መታመኛችሁና አጽናኛችሁ ቅዱስ ሥሉል ሥላሴና ቅዱሳኑ ብቻ መሆናቸውን በድጋሚ አሳይታችሁናል፣ አረጋግጣችሁልናል። ከእንግዲህ ከምድራዊ ኃይል ሆነ፣ 'ቤተ ክህነት' ከተሰኘው የፈሪሳውያን ጎጆ ምንም አንጠብቅም።

እንባዬ ደስታና ሃዘንና ቁጣ የተቀላቀለበት እንባ ነው። ለጊዜው ያን አስቀያሚና የሕዝቤን ደም ያስፈሰሰ ቀይ ቢጫ ኮከብ ሉሲፈራዊ ባንዲራ በአክሱም ጽዮን ባለማየቴ አስደስቶኛል። ለሕዝባችን መጥፎ ዕድል ይዞ የመጣውን ይህን ሉሲፈራዊ የሕወሓት/ቻይና ባንዲራን አቃጥሎ ማስወገድ በተለይ የዲያስፐራው ኃላፊነት መሆን አለበት። እኔ በተቻለኝ አቅምና አጋጣሚ ሁሉ ይህን ከማድረግ አልተቆጠብኩም። ይህ ቀላሉ የቤት ሥራ ነው!

'ካህናቱ፣ ቀሳውስቱና መምህራኑ' ከእግዚአብሔር ቢሆኑ ኖሮ ጊዜ ሳይወስዱ ወዲያው፤ “አለንላችሁ!” ብለው በጸሎት፣ በስብከትና በትምህርታቸው በተደጋጋሚ ባወሱና ሕዝቡን ባነቁ ነበር። እውነት የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ቢሆኑ ኖሮ እናት ቤተ ክርስቲያን አክሱም ጽዮን በጽንፈኛው የጋላ-ኦሮሞ አገዛዝ ሰአራዊት፣ በኤርትራ ቤን አሚርና በሶማሌ አህዛብ ታጣቂዎች ስትጨፈጨፍ፣ ስትራብና ስትዘረፍ ሚሊየን ተዋሕዷውያን '!! ብለው ወደ አደባባይ እንዲወጡና አራት ኪሎን ከብበው እነ ዳግማዊ ግራኝን ለማነቅ ይችሉ ዘንድ ባነሳሷቸው ነበር። ይህ እኮ ሃይማኖታዊ፣ ሃገራዊና ማሕበረሰባዊ ግዴታቸው ነው። አሁንማ ገባን፤ በአህዛብ የዋቄዮ-አላህ መንፈስ ሥር ወድቀዋል፤ ስለዚህ እነርሱ ናቸው ከአህዛብ ጎን ሆነው ሕዝቡን እያስተኙ ወኔ ቢስ እንዲሆን እያደረጉት ያሉት።

አሁን በኅዳር ጽዮን ለሰማዕትነት የበቁትን አባቶቻችንና እናቶቻችንን፣ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችንን ሙሉ ስም ዝርዝር ማወቅ እንፈልጋለን፤ እስካሁን መቆየቱ የከሃዲዎቹ ሕወሓቶች ተንኮል ሊኖርበት ስለሚችል አንድ በአንድ እስከ መጨረሻው ልንታገላቸው ዘንድ ግድ ነው። እነዚህ ከሃዲዎች የሚያገለግሉት ዋቄዮ-አላህ-ሉሲፈርን ነው፤ ስለዚህ እያንዳንዷ 'ተግባራቸው' ለእነርሱ ከተሰጣቸው ዲያብሎሳዊ አጀንዳ ጋር የተቆራኘ ነው። “ወልቃይትንና ራያን አስመልሰናል፤ እልልል! በሉ!” ካሉ በኋላ በሕዝባችን ላይ የተፈጸመውን ግፍ፣ መከራና ዕልቂት ገና የዘር ማጥፋት ጦርነቱን ከጋላ-ኦሮሞዎች፣ ከኤሳያስ አብደላ-ሃሰንና ከበአዴኖችና ወዘተ ቡድኖች ጋር ሆነው ሳይጀምሩ ለነደፉት እባባዊ የ'ሬፈረንድም' ጽንሰ ሃሳባቸው መተገበሪያ ለማደግ አቅደዋል።

አዎ! ወንጀለኞቹ ሕወሓቶች ከሉሲፈራውያኑ የዓለማችን ፈላጭ ቆራጮች የተሰጣቸው ዓላማና ተልዕኮ፤ ከቆሻሻው ዳግማዊ ግራኝ አብዮት አህመድና ጂኒ ጁላ ጋር 'ሰላም አመጣን!' ካሉ በኋላ፤ በስክሪፕታቸው መሰረት ቀጣዩ እርምጃቸው ደግሞ ከኤርትራው ኢሳያስ አብዱላ-ሃሰን ጋር ቀጣዩን 'የሰላም ድርድር አደረግን፤ እልልል! ትግራይ ትስዕር፤ በሉ! ' በማለት 'ታላቂቷን ኢ-አማኒ እንዲሁም የአህዛብና የአረብ ሊግ አባል የምትሆን ኤርትራን' መመስረት፣ የተቀረውን የአክሱም ጽዮናውያን ክፍለ ሃገራት ደግሞ ለአረመኔው ጋላ-ኦሮሞ ማስረከብ ነው። ዝም ጭጭ ብለው ጭፍጨፋውን በመደገፍ ላይ ያሉት ጋላ-ኦሮሞዎች በጣም ቋምጠዋል።

የፀረ-ኦርቶዶክስ ክርስቲያን፣ የፀረ-ኢትዮጵያና የፀረ-ግዕዝ ጦርነቱን የጀመሩትና የሚችሉትን ያህል ክርስቲያን ሕዝቤን ለመጨረስ የደፈሩትም ይህን ዓላማቸውን ለማሳካት ሲሉ ነው። በትግራዩ ጦርነት 'ክርስቲያን፣ ኢትዮጵያዊ፣ አግዓዚ ወይንም ጽዮናዊ' የሆነው የህብረተሰብ አካል ነው በዋናነት የተጠቃው። የቅዱስ ያሬድ፣ የእነ ነገሥታት ካሌብና አፄ ዮሐንስ ልጆች የሆኑትን ነው እየፈለጉ ሲያጠቋቸው የከረሙት፣ በጽዮናዊው የአፄ ዮሐንስ ሰንደቅ ቀለማት ያሸበረቁትን ዓብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት (አክሱም ጽዮን፣ ደብረ ዳሞ፣ ደብረ ዓባይ፣ ማርያም ደንገላት፣ ውቅሮ ጨርቆስ፣ ዛላምበሳ አማኑኤል)ነው በመድፍና በድሮን እንዲመቱ ያደረጓቸው። እግዚኦ!

ስጋታዊው ትንቢቴ ያው እውን እየሆነ ነው፤ ሕወሓቶችን ጨምሮ የዳግማዊ ምንሊክ ፬ኛ ትውልድ መርዛማ ፍሬ የሆኑት ሁሉ ጽዮናውያንን በጣም ነው የሚንቋቸውና የሚጠሏቸው፤ ሁሉም ዋቄዮ-አላህ-ሉሲፈርን ለማንገስ እየሠሩ ነው። ግን ይህ ዲያብሎሳዊ ተልዕኳቸው በጭራሽ አይሳካላቸውም። ኤርትራን፣ ጂቡቲንና በርበራን ጨምሮ ሙሉ ግዛቶቿን ያስመለሰች፣ ታላቋና አክሱም ጽዮናዊቷ ኢትዮጵያ ትመሠረት ዘንድ ግድ ነውና።

የሚያሳዝነውና የሚያስቆጣው እኮ ረሪሃ እግዚአብሔር ያለውን ጽዮናዊ ወጣት በጦርነት ለመፍጀት ከመንደር ወደ መንደር እያዘዋወሩ በአፋርና በአማራ ክልል በድሮን አስጨፈጨፉት፣ የተረፈውን ደግሞ ትግራይን 360 ዲግሪ በመዝጋት በረሃብና በሽታ እንዲያልቅ ማድረጋቸው ነው። ለኢሳያስ አብደላ-ሃሰን ሰላሳ ዓመታት ያህል የፈጀበትን ኤርትራን ከጽዮናውያን “የማጽዳት” ተግባር አረመኔው ዳግማዊ ግራኝ አብዮት አህመድና ደብረጽዮን በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ሊፈጽሙት በቅተዋል። “ችግር – ምላሽ – መፍትሔ / “Problem – Reaction – Solution” + Thesis-Antithesis-Synthesis (ተሲስ ፣ ፀረ-ፀረስታ እና ውህደት/መደመር)

አይይይ! ዓለምም ዝም ያለችው እኮ ለዚህ ነው። ጦርነቱ ግን መንፈሳዊ ነው፤ እርሱንም እየተሸነፉት ስለሆነ ነው ሁሉንም ስጋዊ የሆነ ነገር ሁሉ ተቆጣጥረው ብቻቸውን ያዙን ልቀቁን የሚሉት። ለማንኛውም እነዚህ አውሬዎች የዋቄዮ-አላህ ባሪያዎችና የሉሲፈራውያኑ ወኪሎች ሁሉም ወደ ኤርታ ዓሌ ጥልቅ የመውደቂያቸው ጊዜ መምጣቱን እያየነው ነው። ወዮላቸው!

Sunday, April 5, 2026

Palm Sunday (Hosanna) at Axum, Ethiopia – Jesus Christ is Our Savior and King | ሆሣዕና በአርያም

 


https://www.bitchute.com/video/T1HjLFVyonMO/

https://rumble.com/v783a56-palm-sunday-hosanna-at-axum-ethiopia-jesus-christ-is-our-savior-and-king-.html

ገብርኤል 🧕 ማርያም ኡራኤል ❖ ጊዮርጊስ ተክለ ሐይማኖት መርቆርዮስ ዮሴፍ 

😇 መድኃኔ ዓለም 

🌴 የዘንባባ እሁድ እና በዓለ ሆሣዕና በአክሱም፣ ኢትዮጵያ - ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኛችንና ንጉሣችን ነው

😇 ሆሣዕና በመድኃኔ ዓለም ዕለት መጨረሻ ጊዜ የዋለው ከ፲፩/11 ዓመታት በፊት በ ፳፻፯/2007 .ም ላይ ነበር።

👉 መጪዎቹን ሳምንታትና ወራት በጥሞና እንከታተላቸው!

😇 ሆሣዕና በአርያም | ሰማያዊ ልዑል አምላክ ትሑት ሆኖ ተገለጠ

🌴 ሆሣዕና በአርያም እንኳን አደረሰን 🌴

የሆሣዕና ፳፻፲፫ ዓ.+ የ፳፻፲፪ ዓ.ም ተዓምር በጨረቃ ላይ

🌴 ሆሣዕና በአርያም | ሰማያዊ ልዑል አምላክ ትሑት ሆኖ ተገለጠ 🌴

😇 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ።



🌴 ሰውን ከወደቀበት የበደል ጉድጓድ ያወጣው ዘንድ እግዚአብሔር ክንዱን ወደ ዓለም ላከ፡፡ ሰው ሆኖ የተገለጠው የእግዚአብሔር ክንድ በጉድጓድ ተጥሎ የነበረን በዚያም በሥጋ በነፍስ፤ በውስጥ በአፍአ ቆስሎ የነበረ አዳምን በትህትና ሁለተኛ አዳም ሆኖ በሥጋ የቆሰለውን በለበሰው ሥጋ ቆስሎ;በነፍስ የታመመውን በትምህርት አዳነ፡፡ ከእርሱ አስቀድሞ ሰውን ከሞት ወደ ሕይወት፤ ከባርነት ወደ ነፃነት የሚያመጣ ባለመኖሩ እርሱ ሁሉን የፈጠረ ሁሉን የሚያኖር እግዚአብሔር ሰው ሆኖ ለሰው መድኃኒት ሆነ፡፡ በሞቱም መድኃኒትነትን አሣየ፡፡ በነብይ መድኃኒተ ፈነወ እግዚአብሔር ለሕዝቡ፤ እግዚአብሔር ለሕዝቡ መድኃኒትን ሰደደ፡፡ (መዝ.፻፲፥፱) ተብሎ የተነገረው ተፈጸመ፡፡

ክርስቶስ ባለ መድኃኒት ሆኖ በኃጢአት ለታመሙ ደቂቀ አዳም ሁሉ ሕይወትን ይሰጥ ዘንድ ወደዚህኛው ዓለም መጣ፡፡ በምድራዊ ሥርዓት እንደምናየው መድኃኒትና ባለ መድኃኒት እንደሚለያዩ አይደለም፡፡ ሁለቱንም እርሱ በመምጣቱ (ሰው በመሆኑ) ፈጸመ እንጂ፡፡ መድኃኒት አድርጎ ሥጋውን ደሙን የሰጠ እርሱ ነው፡፡ በካህናት አድሮ ሰው በንስሐ ሲመለስ መድኃኒት ወደሆነው ወደ ራሱ የሚመራ እርሱ ነው፡፡

ክርስቶስ መድኃኒት መሆኑ በሕማሙ እና በሞቱ ነው፡፡ በእመቤታችን ማኅፀን የተጀመረው የእርሱ መድኃኒትነት እና ፍቅሩ ፍፃሜውን ያገኘው በሕማሙ እና በሞቱ ነው፡፡ መሐሪ ንጉሥ እርሱ መሆኑን ይገልጥ ዘንድ በፈቃዱ ወደ ኢየሩሳሌም መጣ፡፡ ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም ከመግባቱ አስቀድሞ ከኢየሩሳሌም ፲፮ ያህል ምዕራፍ በምትርቀው በቤተፋጌ ከደቀመዛሙርቱ ጋር ነበር፡፡

ከደቀ መዛሙርቱም ሁለቱን (ማለትም ጴጥሮስን እና ዮሐንስን) በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ ወዲያውም ወደ እርሷ ገብታችሁ ከሰው ማንም ገና ያልተቀመጠበትን ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ ፈትታችሁ አምጡልኝ፡፡ (ማር ፲፩፡፪) በማለት አዘዛቸው፡፡ ዳግመኛም ሰው ወዳልገባባት የተዘጋች የምሥራቅ ደጅ ወደ ምትባል ወደ ድንግል መጥቶ ዘጠኝ ወር ማኅፀኗን ከተማ አድርጎ እንደኖረ፤ ማኅየዊት ከምትሆን ሕማሙ በኋላም ሰው ባልተቀበረበት መቃብር እንደተቀበረ፤ አሁንም ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም ለመግባት ማንም ሰው ያልተቀመጠባቸውን በሌላ መንደር የሚገኙ አህያንና ውርንጫን እንዲያመጡ ደቀመዛሙርቱን አዘዘ፡፡

የፍጥረት ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በልደቱ እስትንፋሷን የገበረችለትን አህያ አሁን ደግሞ በፈቃዱ ስለ ሰው ሁሉ ሊሞት ሲል ንጉሥነቱን ሊያስመሰክርባት ወደደ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ካለው ፲፮ ምዕራፍ አሥራ አራቱን በአህያ ላይ ሳይቀመጥ በእግሩ ሄደ፡፡ ከዚያም ሁለቱን ምዕራፍ በአህያ ላይ በመቀመጥ ከተጓዘ በኋላ የኢየሩሳሌምን መቅደስ ሦስት ጊዜ በውርጫዋ ላይ በመሆን ዞረ፡፡ በዚህም ለሰው ሁሉ ያለው ቸርነቱ፣ ሕግ የተሰጣቸው አይሁድ እና ሕግ ያልተሰጣቸው አሕዛብ ላይ እኩል ቀንበርን መጫን እንዳይገባ አጠየቀ፡፡

ወደ ኢየሩሳሌምም ሲሄድ ብዙ ሰዎች ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፣ ሌሎችም ከዛፍ ቅጠሎችን እየቆረጡ ያነጥፉ ነበር፡፡ (ማር.፲፩፡፰)፡፡ ከዚያም ሰዎች ሆሣዕና በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው (ማር.፲፩፡፱) በማለት አመሰገኑ፡፡ ይህም ዛሬ ለቤተ ክርስቲያን እኛ ክርስቲያኖች ቡሩክ ስሙ ለእግዚብሔር ወቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር፤ የእግዚአብሔር ስሙ ምስጉን ነው፡፡ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ እርሱ ክርስቶስም ምስጉን ነው በማለት የአብ እና የወልድን መስተካከልን ገልጸን ጌታን እናመሰግናለን፡፡ ጌታን የሚከተሉት ሰዎች ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር (ማር.፲፩፡፲) ይኸውም በልዕልና፣ በሰማይ ያለ መድኃኒት፣ ከሰማይ የመጣ መድኃኒት ማለት ነው፡፡

የእግዚአብሔር ፍቅር እና መሓሪ መሆን በክርስቶስ ሕማም እና ሞት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተገልጧል፡፡ ክርስቶስ የተቀበለው ሕማም እና ሞት የእርሱን አምላክነት እና ንጉሥነት አልሸሸገውም፡፡ እንደውም ዙፋኑን መስቀል በማድረግ ንጉሥነቱን በመድኃኒትነቱ ገልጿል እንጂ፡፡ በነብይ እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፣ እግዚአብሔር ከዓለም አስቀድሞ ንጉሥ ነው፤ በምድር መካከልም መድኃኒትን አደረገ መዝ. ፸፫፤፲፪ ተብሎ የተነገረው እግዚአሔብር ድኅነትን በፈጸመበት ማዕከለ ምድር ሲሰቀል በመድኀኒትነቱ ንጉሥነቱን መግለጡን ያመለክታል፡፡ ዳግመኛም አንሰ ተሰየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ በጽዮን በደብረ መቅደሱ፤ እኔ ንጉሥ ሆኜ ተሸምኩ በተቀደሰው ተራራ ላይ(መዝ.፪፡፮) ተብሎ የተነገረው ኦርቶዶክሳውያን አበው እነርሱ (አይሁድ) ሰቅለነው ገድለነው ኋላ ፈርሶ በስብሶ ይቀራል ይሉኛል እንጂ እኔ ደብረ መቅደስ በምትባል በመስቀል ላይ ነግሻለሁ በማለት ይተረጉሙታል፡፡

ጌታ ንግሥናው ክብሩ የተገለጠበት ሆነ እንጂ መታመሙ እና መሞቱ ውርደት ክብሩንም የሚሸሽግ አይደለም፡፡ ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ ይትባረክ እግዚአብሔር ዘሰመየ ሕማማት ወልዱ ክብረ ወስብሐት፣ የልጁን ሕማማት ክብርና ምስጋና አድርጎ የሰየመ እግዚአብሔር ይመስገን አለ፡፡ እኛን ያከበረበት በመሆኑ ሕማሙ ክብር እንደተባለ እናስተውል፡፡ በመስቀል ላይ ሆኖም በቀኝ የተሠቀለው ወንበዴ አቤቱ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ (ሉቃ ፳፬ )በማለት ንጉሥነቱ መስክሮለታል፡፡ ለዚህ ነው ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም በምስጋና መግባቱ መድኃኒትነቱን እና ንጉሥነቱን ያሳያል ያልነው፡፡ ዳግመኛም ሁሉን የያዘ ጌታ በአህያ ላይ መቀመጡ ትህትናው ያስረዳል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል ዲባ ዕዋለ አድግ ነበረ፡፡ በማለት ሰማያዊ ልዑል አምላክ ትሑት ሆኖ እንደተገለጠ ተናገረ፡፡

ጌታ ከመድኃኒትነቱ የተነሣ ድንቅ የሆኑ እና ተአምራትን ለሰዎች አሳየ (ገለጠ)፡፡ እም ሆሳዕናሁ አርአያ ተአምረ ወመንክረ (ቅዳ. ጎርጎ.ዘኑሲስ) እንዲል፡፡ ይኸውም በአህያ ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ አእምሮ ጠባይዕ ያልቀናላቸው ሕፃናት ዕውቀት ተገልጾላቸው ሆሳዕና በአርያም እያሉ ጌታ በማመስገናቸው ነው፡፡ ዳግመኛም በከሃሊነቱ መናገር ለማይችሉ ዕውቀት ለሌላቸው ድንጋዮች ዕውቀት ተሰጥቷቸው መናገር ችለው ጌታን አመስግነዋል፡፡ እርሱ የባሕርይ አምላክ መሆኑ በሰውነቱም ቀድሞ በበደል ምክንያት ለሰው ከመገዛት ውጪ የሆኑ ፍጥረታት ዳግመኛ በሥጋዌ ለሰው እንደተገዙ ከዚህ ሁሉ ማስተዋል ይገባል፡፡

ጌታ ከመድኃኒትነቱ የተነሣ ልጅነት እና ተአምራት ማድረግን ገለጸ፡፡ እም ሆሳዕናሁ አርአያ ጸጋ ወኅይለ እንዲል (ቅዳሴ ጎርጎ. ዘኑሲስ)፡፡ የእርሱ ማዳን ከሰው ተወስዶበት የነበረ የጸጋ ልጅነት እንዲመለስለት አድርጋ በልጅነት ላይ ገቢረ ተአምራት (ተአምራትን ማድረግ) ገልጿል፡፡ ይኸውም እርሱ በረድኤት አድሮባቸው ድንቅ ተአምራትን ለሚያደርጉ ቅዱሳን መሠረት ነው፡፡ በተጨማሪም ልጅነትን ካገኙ በኋላ በበደል ሲገኙ ለንስሓ የሚሆን እንባን ሠጠ፡፡ እምሆሳዕናሁ ወሀበ ፈልፈለ አንብዕ ለኅጥአን እንዲል (ቅዳሴ ጎርጎ. ዘኑሲስ) ይኸውም የበደሉትን ያከብራቸው ዘንድ፣ ኀጥአንን ከኃጢአታቸው ያነጻቸው ዘንድ እንዲሁም የሳቱትን በንስሐ ይመልሳቸው ዘንድ ነው፡፡

ዳግመኛም ጌታ መድኀኒት ከመሆኑ የተነሣ ለዕውራን ዳግመኛ ብርሃንን ሰጠ፡፡ ይኸውም ለጊዜው በተፈጥሮ ዐይን ተሰጥቷቸው የታወሩትን ፈውሶ በሥጋ ብርሃን መስጠቱ ሲሆን፤ ፍጻሜው ግን በነፍስ ዕውቀትን ከማጣት የተነሣ ዕውራን የነበሩትን ትምህርትን; ዕውቀትን ገለጸላቸው፡፡ ይኸውም የእርሱ ገንዘቡ ስለሚሆን አንድነት ሦስትነት፣ አምላክነቱን መድኃኒት መሆኑን ገለጠላቸው ማለት ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

🌴 Hosanna (Hosa'ina) is one of the major feasts in the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, commemorating Jesus Christ’s triumphal entry into Jerusalem.

🌴The celebration of "Hosanna, Savior of the World" is primarily observed on Palm Sunday, the Sunday before Easter, which commemorates Jesus Christ's triumphal entry into Jerusalem. It marks the beginning of Holy Week, transitioning from the joyful shouts of "Hosanna" to the solemnity of the Passion.

Significance of the Celebration

Meaning of Hosanna: The term "Hosanna" is a Hebrew expression meaning "save us now" or "please deliver us". While originally a plea, it became a shout of praise and adoration, acknowledging Jesus as the Messiah and Savior.

  • The Triumphal Entry: Jesus entered Jerusalem riding on a donkey, fulfilling the prophecy of Zechariah 9:9, which portrays a righteous, victorious, yet humble king.

  • "Savior of the World": The celebration highlights Jesus as the ultimate deliverer not just from political oppression, but from sin and death.

  • Palm Branches: Waving palms represents victory, peace, and eternal life.

♰ Themes of Reflection

  • Humility vs. Pride: Jesus’ entrance on a humble donkey rather than a warhorse symbolizes a kingdom based on peace and service rather than power.

  • The Fickleness of the Crowd: Palm Sunday highlights the irony that the same crowd shouting "Hosanna" soon turned and cried for his crucifixion, prompting self-reflection on faith and commitment.

  • A Call for Current Salvation: Modern celebrations use "Hosanna" as a continued prayer for salvation from modern challenges like social conflict, war, and spiritual dryness.

Hosanna in Axum is a vibrant Ethiopian Orthodox celebration of Palm Sunday, occurring the Sunday before Easter to mark Jesus’ entry into Jerusalem. It features massive, colorful processions, specifically at the St. Mary of Zion Church, where followers wear palm leaf headbands and deacons distribute palm branches.

🌴 Key Aspects of the Celebration:

  • Location: The celebration is famously observed at St. Mary of Zion Church in Axum.

  • Traditions: Participants wear rings and headbands made of palm leaves, symbolizing the branches laid before Jesus.

  • Procession: The event includes colorful, long-running processions filled with chanting and joyous praise, typically in late March or April.

  • Significance: It serves as the start of Holy Week, with pilgrims and locals gathering to honor the event with immense faith.

Although recent years have seen smaller turnouts due to regional instability, the celebration remains a vital, peaceful, and deeply traditional event in the city.

♰ Medhane Alem (Holy Savior of the World)

Adi Kesho Rock-hewn Church, 4th Century.– Tigray, Ethiopia

♰ Medhane Alem Adi Kesho (Holy Savior Church at Adi Kesho) in the Tigray region of Ethiopia.

♰ Key details about the church:

  • Location: Tigray Region, Gheralta area.

  • Significance: It is considered one of Tigray's oldest and finest rock-hewn churches.

  • Architecture: It features a unique decorated narthex, six huge square pillars supporting the ceiling, and intricate reliefs and geometrical patterns.

  • History: The church is often described as having an immense height and massive pillars, bearing a resemblance to a cathedral.

Medhane Alem Adi Kesho is one of Tigray's oldest and most remarkable rock-hewn churches, estimated to date 4th century. Located approximately 6 kilometers off the gravel road from the Wukro to Adigrat highway near the small town of Tekatesfay, this church is renowned for its architectural and historical significance.

An unusual feature of Medhane Alem Adi Kesho is the beautifully decorated narthex connecting the northern and southern ends of the church. Two doors lead to the interior, where the ceiling is supported by six massive square pillars. The ceiling is adorned with reliefs and geometrical patterns, and due to its immense height and substantial pillars, the church resembles a cathedral. Engravings on the walls include a croix patêe on the right side of the back wall.

The church's exterior and interior walls are roughly hewn, and it features a unique mechanism for unlocking the doors from both inside and outside. Inside, different pillars carved out of the rock are stained with honey and milk, stemming from local tradition that deems the church itself to have healing powers. When people are sick, they consume milk or honey off the church’s columns.

Surrounded by a variety of indigenous plants, the area remains lush and vibrant, adding to the church's serene atmosphere. Visitors often note that the journey to reach the site offers an enjoyable walk with stunning views, making the visit to this unique church an unforgettable experience.

Overall, Medhane Alem Adi Kesho stands as a testament to Ethiopia's rich religious heritage and architectural ingenuity, offering insight into the country's historical devotion and cultural practices.

♰ Miskaye Hizunan Medhane Alem (Holy Savior) Monastery, Addis Ababa, Ethiopia, 1950

Miskaye Hizunan Medhane Alem Monastery in Addis Ababa is

a prominent Ethiopian Orthodox Tewahedo Church institution, known as a significant training center for clergy, monks, and youth, often hosting thousands of Sunday school students. It is a renowned monastery located in the capital, often associated with training.

♰ Key Details regarding Miskaye Hizunan Medhane Alem

  • Role: Known as a key training center for priests, monks, and Sunday school students.

    Location: Situated within the Addis Ababa region.

  • Significance: Serves as a major monastery church with a large congregation of young people, hosting over 12,000 Sunday school students (males and females).

  • "Miskaye Hizunan" is of Ethiopian origin. The meaning of "Miskaye Hizunan" is a shelter for the afflicted , which is known as "Yehazentegnoch Metteleya" (የሐዘንተኞች መጠለያ) in Amharic language.


Israel's 'Christian Hate Crime': After Smashing a Statue of Jesus, Now a Nun Assaulted in Jerusalem

https://www.bitchute.com/video/lPnG1s8N2RV6/ https://rumble.com/v799igu-israels-christian-hate-crime-after-smashing-a-statue-of-jesus-now-a-...