Showing posts with label ጽዮን. Show all posts
Showing posts with label ጽዮን. Show all posts

Tuesday, May 19, 2026

The Disappearance of Saint Yared The Melodious: The Great Ethiopian Christian Composer

https://www.bitchute.com/video/KQmzqw0UpmB5/

https://rumble.com/v7a2gwe-the-disappearance-of-saint-yared-the-melodious-the-great-ethiopian-christia.html

😇 እንኩዋን ለታላቁ ሊቅ "ቅዱስ ያሬድ" ዓመታዊ በዓል አደረሰን ✞✞✞

የዛሬው ግንቦት ፲፩/11 ዕለት ቅዱስ ያሬድ የተሰወረበት አመታዊ ክብረበዓል ነው።

😇 Today, Ginbot ፲፩/11, ፳፻፲፰/2018 (May 19, 2026) marks the departure of St. Yared, the great Ethiopian composer, Saint Yared, who disappeared at the age of 66.

😇 Saint Yared, the legendary 6th-century Axumite composer credited with creating the liturgical music and chant tradition (Zema) of the Ethiopian and Eritrean Orthodox Churches, is believed by tradition to have disappeared rather than died.

His disappearance is surrounded by rich spiritual tradition:

The Departure: On May 19, 571 AD (Ginbot 11 on the Ethiopian calendar), after serving the church and praising God, Yared sought to withdraw from the world. According to hagiography, he stood before the Tabernacle of Zion in Axum and prayed, after which he was raised above the ground and transported away.

The Location: He is said to have departed to the desert and the mountains, specifically living a life of fasting and prayer in the wilderness. Some traditions state he spent his final days in the Debre Hawi monastery in the northern mountains.

Legacy: The exact location of his grave remains unknown to this day. His monumental contributions—including the development of the Digua (hymn books) and a unique musical notation system—are commemorated annually by the church on his feast day.

🎶 Long Before This Form of Musical Notation Began in The West, There Was a Composer in Ethiopia

https://www.bitchute.com/video/CA961Pd6HnnR/

😇 The First Great Master of The Style Was The Composer Saint Yared

https://www.bitchute.com/video/Okr1PZVGZayJ/

🐦 Three Little Birds: Saint Yared’s Inspiration From Above

😮 ልዩና ብሩክ በሆነው በዛሬው ዕለት አንድ ያስገረመኝ፣ ያስደሰተኝና ለሤረኞቹ ያሳዘነኝ ክስተት፤ በ'አዲስ ኢትዮጵያ' ዩቲውብ ቻነሌ ከአራት ዓመታት በፊት በፍልሰታ ዕለት ልኬው የነበረውን ቪዲዮ ሤረኞቹ የፋሺስቱ ጋላ-ኦሮሞ እስላማዊ አገዛዝ ባሪያዎች ማስነሳታቸውና 'ኮፒ ራይት ስትራይክ' ማሰጠታቸው ነው። ሆን ተብሎ ልክ በቅዱስ ያሬድ ዕለት። ስለ ሤረኛው ጋላ-ኦሮሞ አጋራቸው ስለ 'እፎይ' ማስጠንቀቅ በመጀመሬ... በቪዲዮው የዘማሪ 'ቀሲስ' እንግዳወርቅ በቀለ 'ደጅ ጠናሁ ሜዲያ'(ኦሮማራ ወይም ጋላ-ኦሮሞ ነውን?) አንድ መዝሙር ስለገባበት ፈልፍለው በማውጣት ስትራይክ አስጡት! አይይይ! በአክሱማዊቷ ኢትዮጵያ ላይ ጀነሳይዳዊ ጂሃድ በመክፈት ከሚሊየን በላይ የቅዱስ ያሬድን ልጆችን መጨፍጨፉ አልበቃቸውም ያው በማህበራዊ ሜዲያም ቤተሰቦቹን በዚህ መልክ ማሳደዱን ቀጥለውበታል። ከሰባት ዓመታት በፊት ብዙ ተከታዮች የነበሩትን የቀደመውን የ'አዲስ ኢትዮጵያ' ቻኔል ልክ በፋሲካ ትንሣኤ ዕለት ያስነሱትም እነ 'ቋንቋየነሽ፣ ዘመድኩን በቀለ፣ 'አቡነ' ፋኑኤል' ነበሩ። ለእኔ ትልቅ ምልክት ነው፤ ደስ ብሎኛል...ለእነርሱ ግን ወዮላቸው! ወዮላቸው! ወዮላቸው!




የጻድቁ አባታችን የቅዱስ ያሬድ ረድኤትና በረከት ከሀገራችን ከኢትዮጵያና ከህዝቧም ጋር ይሁን አሜን።

አበው ቅዱስ ጳውሎስ በሁለተኛ ቆሮንቶስ መልዕክቱ ላይ "እንዲህ ያለው ሰው ከአሥራ አራት ዓመት በፊት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ ተነጠቀ ። እንዲህ ያለውንም ሰው አውቃለሁ ። በሥጋ እንደ ሆነ ወይም ያለ ሥጋ እንደሆነ አላውቅም ። እግዚአብሔር ያውቃል ። ወደ ገነት ተነጠቀ ። ሰውም ሊናገር የማይገባውን ፤ የማይነገረውን ቃል ሰማ ።"2ቆሮ. 122-5 ብሎ የተናገረው ለቅዱስ ያሬድ ነው ብለውም ይተረጉሙታል ።

ግዕዝ ፣ እዝል ፣ ዓራራይ ተብለው የተወሰኑ ሰማያዊ የዜማ ስልቶችንም የተማረው ከእግዚአብሔር ነው ። ሊቁ ማኅሌታይ ወደ ምድር ተመልሶ በታላቅ ተመስጦ አክሱም ጽዮን ማርያም ውስጥ በሃሌታ አመሰገነ ። ሕዝቡና ንጉሡም አፄ ገብረ መስቀል ከዜማው ጣዕም የተነሳ አደነቁ ። ቅዱስ ያሬድ ዜማውን በንጉሡ ፊት ሲያቀርብ ንጉሡ በተመስጦ እግሩን በጦር ቢወጉትም የዜማው አቅራቢው ቅዱስ ያሬድም ሆነ ዜማውን የሚሠሙት ንጉሥ ገብረ መስቀል ዝማሬው እስኪያልቅ ድረስ የተፈጠረውን አደጋ አላዩትም ነበር ። ሁሉም በተመስጦ ላይ ነበሩና ።

የቅዱስ ያሬድ ዜማዎች በህግ የሚዜሙ ባለምልክቶች ናቸው። ምልክቶቹ «ኖታ» ከሚባለው የአውሮፓውያን የዜማ ስልት ጋር ይወዳደራሉ ። ከላይ እንደተገለጸው ሊቁ የደረሳቸው የዜማ አይነቶች ግዕዝ፤ እዝል እና አራራይ በመባል ይታወቃሉ። ሶስቱም ዜማዎች መሀትው ዋዜማ፤ ስልጣን፤ እስመለአለም፤ አቡን ቅንዋትና ሰላም የሚባሉ መጠሪያ ስሞችም አሏቸው። ዜማዎቹ ልዩ ልዩ ስልቶችን የያዙ ሲሆን አጫብር፤ ቆሜ፤ አሮጌ ቤተልሄም፤ አዲስ ቤተልሄምና ተጉለቱ በመባል ይታወቃሉ።

የዜማዎቹ ስልቶች በተለያዩ ድምፆች፣ በጭንቅላት፣ በአፍንጫና በጉሮሮ ይዜማሉ። በዚህ ሂደትም አራተኛ አቋቋም የሚባለው ስልት ጥሩ የዜማ መገለጫ ስለመሆኑ በዘርፉ በጥናት ውስጥ ያለፉ ሊቃውን አባቶች ይመሰክራሉ። ይህ ዜማ ታች ቤት፣ ላይ ቤት፣ ሳንኳና ተክሌ ሰቆጤ በሚሉ መጠሪያዎች በተለይ በጎንደር አካባቢ ጥቅም ላይ እንደሚውል ይነገራል።

በቅዱስ ያሬድ የዜማ ስልት የሚቃኙት ካህናትም በዝማሜ በመረገድ፤ በፅናፅልና በከበሮ ያሸበሽባሉ። የዘንጋቸው አወዛወዝና አጣጣል የፅናፅሉ አወራረድና አመላለስ እንዲሁም የከበሮ አመታቱ በሦስት የተከፈለ ሲሆን መደበኛ ስሞቹም ንዑስና ዓብይ፣ መረግድ፣ ድፋት ለዘብና ማህሌተ ገንቦ ይባላሉ። አእምሮን ከሚያነቃቁና መንፈስን ከሚማርኩ ዜማዎች መካከልም በተለይ ለዘብና ማህሌተ ገንቦ የተሰኙት ዝማሬዎች እጅግ ጥዑም የሆኑና ለሚሰማውም ደስ የሚያሰኙ የዜማ ስልቶች ናቸው።

ድጓ ፣ ጾመድጓ ፣ ምዕራፍ ፣ ዝማሬና መዋሰዕት የተባሉ አምስት መጻሕፍትን ደርሶ ለቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያበረከተው ቅዱስ ያሬድ ታላቅ ደራሲም ነው ። ሊቁ ማኅሌታይ፤ ጥዑመ ልሳን ፣ ንሕብ ፣ ሊቀ ሊቃውንት ፣ የሱራፌል አምሳያ ፣ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ ፣ ካህነ ስብሐት፣ መዘምር ዘበድርሳን ፣ ማኅሌታይ ፣ ልዑለ ስብከት እያሉ የሚጠሩት ሊቁ ማኅሌታይ በአክሱም ጽዮን እና በደብረ ዳሞ አገልግሏል ። በጣና ቂርቆስ እና በዙር አባ አቡነ አረጋዊ ገዳምና በሌሎች የኢትዮጵያ ገዳማትም ወንበር ዘርግቶ ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል ።

ቅዱስ ያሬድ ለመጀመሪያ ጊዜ ያዜመው «ሀሌ ሉያ ለአብ፣ ሀሌ ሉያ ለወልድ፣ ሀሌሉያ ለመንፈስ ቅዱስ፣ በቀዳሚ ገብረ እግዚአብሔር ሰማየ ወምድር፣ ወበዳግም አርእዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ሲል ነበር። ይህን ዜማ ሲቀኝም ህዝቡ እሱን ለማዳመጥ ሀገር አቋርጦ ይመጣ እንደነበር መዛግብት ያስረዳሉ። ይህ ሁኔታም ያልተለመደ በመሆኑ እንደትንግርት ይቆጠር ነበር። የዜማው አወራረድ ተሰምቶ አይጠገብም። በዘመኑ የነበሩት ንጉሥ አፄ ገብረ መስቀል በቅዱስ ያሬድ መንፈሳዊ ዜማ በመደነቃቸው ዜማው በአዋጅ ጸድቆ ሥራ ላይ እንዲውል መፍቀዳቸው ይነገራል።

ያሬድ የንጉሡ የቅርብ ሰውና ወዳጃቸውም ነበር። እሳቸውም ሹመት ሊሰጡት ደጋግመው ጠይቀውታል። ይሁን እንጂ መንፈሱ በምናኔና ዓለምን በመናቅ የተሞላ ስለነበር ጥያቄያቸውን ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆነም። አንድ ቀን ግን ጻድቁ ቅዱስ ያሬድ ንጉሡን «በምናኔ በሰሜን ገዳም እንድኖር ይፍቀዱልኝ» ሲል ጠየቃቸው። እርሳቸውም ሀሳቡን ተቀብለው ፈቀዱለት። ቅዱስ ያሬድ በአክሱምና በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም ለረጅም ጊዜያት በትጋት ደቀ መዛሙርትንም በማፍራት አገልግሏል ።

ጻድቁም ወደ ሰሜን ተራሮች ወደ ራስ ደጀን ከመሄዱ በፊትም ታቦተ ጽዮንን ለመሰናበት ከመቅደስ ገባና ከመሬት ክንድ ከስንዝር ከፍ ብሎ በመቆም ዛሬ ሁላችን በውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ መጨረሻ ላይ የምንጸልየውን "አንቀፀ ብርሃን" የሚባለውን የምስጋና ጸሎት ንባቡን ከነ ዜማው ደርሶ ለቤተ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አበረከቶልን ከንጉሥ አፄ ገብረመስቀል ፈቃድ ያገኘው ጻድቁ ቅዱስ ያሬድም የመጨረሻዎቹን የዚህ ምድር ላይ ቆይታውን በሰሜን ተራሮች አካባቢ በበረዶማው የራስ ደጀን ተራራ ላይ ለማድረግ ሄዷል ። በዚያም በዋሻ ተቀምጦ በትጋሃ መላእክትና በተባሕትዎ በድንግልና ሲያገለግል ፤ ተተኪ ደቀመዛሙርትንም ሲያፈራ ቆይቶ በመጨረሻም ግንቦት 1 ቀን በ576 ዓም በተወለደ በ71 ዓመቱ ተሰውሯል።

አሳዛኙ ነገር እንዲህ ያለው ሊቅ ፣ ጻድቅና ቅዱስ የዜማና የመጻሕፍት ደራሲ የሆነው አባት ቅዱስ ያሬድ በሀገሩ በኢትዮጵያ የቀድሞው መንግሥት በስሙ ከሰየመለት የሙዚቃ ትምሕርት ቤት በቀር በክብሩ መጠን የተደረገለት አንድም ማስታወሻ የሚሆን ነገር በሀገሩ ላይ የለም ። ይህ የሆነው ደግሞ የቅዱስ ያሬድም ሆነ የኢትዮጵያ ሊቃውንት ትልቁ በደላቸው ኢትዮጵያዊ በመሆናቸው ብቻ ነው ።

አቤት አቤት ቅዱስ ያሬድ አውሮፓዊ ቢሆን ኖሮ ብዬ ሳስብ ምን ሊያደርጉት እንደሚችሉ መገመት ብቻ ነው ። መንገዱ ፣ አደባባዩ ፣ ተራራው ፣ ትምህርት ቤቱ ፣ ቁሳቁሱ ሳይቀር በስሙ በተሰየመ ነበር ። አንድ ፒያኖ ይዘው ኦርኬስትራ ለመሩ ሰዎች ተአምር ለመፍጠርና ስማቸውን በመሸጥ የሀገር ገቢ ማግኛ ሲያደርጉ ሳይ እደነቃለሁ ። በጀርመን ሀገር በቦን ከተማ የቤትሆቨን ቤትን ለመጎብኘት ሄጄ ቅዱስ ያሬድን ሳስበው አልቅስ አልቅስ ነበር ያለኝ ። ሰው ቢልዮን ዶላር የሚያስገባለትን ሀብት ከመጋረጃ ጀርባ ደብቆ እንዴት በድህነት ይማቅቃል?? በቅዱስ ያሬድ አፍሮ በማያውቀው ፑሽኪን ይመጻደቃል ።

ኢትዮጵያ ለማታውቀው ፑሽኪን ለተባለ ሩሲያዊና ደጎል ለተባለ እንግሊዛዊው ግለሰቦች አደባባይ ስትሰይም ፣ ለአቶ ቸርችል ጎዳና ፣ ለጀናራል ዊንጌት ደግሞ ትምሕርት ቤት በመሥራትና በመሰየም ያልበላትን ስታክ ትታያለች ። በአቡነ አረጋዊ ስም ቡና ቤት ፣ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቢራ ለመሰየም ግን ቅሽሽ አይላትም ፤ የሚጠየፍና ሃይ ባይም ትውልድ የለም ።

አንድ የውጭ ሀገር ሰው ኢትዮጵያ ሄጄ ስለ ቅዱስ ያሬድ ላጥና ቢል መከራውን ነው የሚበላው ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በሕይወት ለመኖሯ እና በምድር ላይ እንድትቀጥል ካደረጓት ነገሮች አንዱና ዋነኛው የቅዱስ ያሬድ ሥራዎች መኖር ነው ። ያለ ቅዱስ ያሬድ ሥራዎች ቤተክርስቲያናችን ማሰብ በራሱ ከባድ ነው የሚሆነው ። ቅዱስ ያሬድ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ፣ ለሊቃነ ጳጳሳቱ ፣ ለካህናትና ለዲያቆናቱ ፣ ለመዘምራኑም ሁሉ ፤ ሞገስ ፣ ክብር ፣ እንጀራም ጭምር ነው ። ነገር ግን ይኽን ሁሉ ለሆነላቸው ጻድቅ አንዳቸውም አስታውሰው ግዙፍ ነገር በስሙ ሊሠሩ ሲነሳሱ አይታዩም።

🎶 እነ ሞዛርት ከመወለዳቸው ሺህ ዓመታት አስቀድሞ፡ ሊቁ ማኅሌታይ አባታችን ቅዱስ ያሬድ በአክሱማዊቷ ኢትዮጵያችን ተወለደ

😇 ስለ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አብዛኛው ይህ ሥጋዊ ዓለም ምንም እውቀት የለውም/ማወቅም አይፈልግም። ምክኒያቱም፤ ቅዱስ ያሬድ በመንፈሳዊው ዓለም ብቻ ሊሰማ የሚችል እጅግ በጣም የተራቀቀ የዜማ ጥበብ አባት በመሆኑ ነው። ሥጋውያኑ ኤዶማውያኑ አፍሪካዊው/ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ የእነ ሞዛርትን እና ቤትሆቨንን ቦታ የሚነጥቅባቸው ከእነርሱ የላቀ የዜና ደራሲ፣ አቀናባሪ እና ምሁር ሆኖ ስላገኙት ነው። የመንፈሳዊ ማንነትና ምንነት ቢኖራቸው ኖሮማ በየሙዚቃ ትምህርት ቤቱ ስለ ቅዱስ ያሬድ ውብ ዜማዎችን እና ማስታዎሻዎቻቸውን ባስተማሩ ነበር። በተገላቢጦሽ ግን የእኛ ትምህርት ቤቶች የአውሮፓውያኑን ያስተምራሉ።

ቅዱስ ያሬድ:- ከእግዚአብሔር ያገኘነው አባታችን፤

ክብራችን: ሞገሳችን ነውና በምን እንመስለዋለን? አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም): ልቡናው የቅድስና ማሕደር: ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ ነው። እስከ አርያም ተነጥቆ የማይፈጸም ምሥጢርን የተመገበ ማን እንደርሱ!

ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮዽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከራስ ጸጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ: ሙሉ አካሏ ነው። ታዲያ በተለይ በእነዚህ በያዝናቸው አራት ዓመታት ከባዕዳውያኑ ኤዶማውያኑ እስማኤላውያን እና ከዋቄዮ-በዓል-አላህ-ባፎሜት-ሉሲፈር ባሪያዎች ጋር አብራችሁ በ ቅዱስ ያሬድ ትውልድ ከተማ በቅድስት አክሱም ጽዮን ላይ የዘመታችሁ ሁሉ ዛሬም የመመለስ ጭላንጭል እንኳን እያሳያችሁ አይደለም፤ የንሰሐው ጊዜም እያለቀባችሁ ነው፤ እንግዲህ ወዮላችሁ! ወዮላችሁ! ወዮላችሁ!

አውሮጳውያኑ የዜማ ሊቃውንት ሞዛርትና ቤትሆቨን ከመወለዳቸው ሺህ ዓመታት አስቀድሞ በኢትዮጵያችን የተወለደ ነው ሊቁ ማኅሌታይ አባታችን ቅዱስ ያሬድ። ጻድቁ የተወለደው በ ፭፻፭/ 505 /ም አክሱም ጽዮን አቅራቢያ ሲሆን አባቱ ይስሐቅ (አብድዩ ) እናቱም ክርስቲና (ታኡክልያ) ይባላሉ።

ይህን ዘመን በጥሞና ልናጠናው ይገባናል። በእኔ በኩል እንደሚታየኝ፤ አክሱማዊቷ ኢትዮጵያ በዚህ ዘመን (ንጉሠ ነገሥታት አብርሐ እና አጽበሐ፣ ንጉሥ ካሌብ...) ነበር በሁሉም መስከ ከፍታዋ መታየት ጀምሮ የነብረው። በሃይማኖት እና መንፈሳዊ ሕይወት፣ በሥነ ጥበብ፣ ሥነ ጽሑፍ እና ዜማ ፥ በምጣኔ ኃብት፣ እርሻ እና ንግድ፣ በሕንፃ፣ ዋሻ እና መርከብ ግንባታዎች ሮማውያኑን እና አጋሮቻቸውን ያስደነቁ፣ ያስቀኑ እና ያስፈሩ ነበሩ። ስለዚህ የምስራቅ ሮማ (ቁስጥንጥንያ) ነገሥታት አክሱማዊቷን ኢትዮጵያ ለማዳከም ያልጠነሰሱት ሤራ አልነበረም። ይህም ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ በኋላ ላይ ከፍተኛ ውድቀትን፣ መራቆትን፣ ድኽነትን፣ ክፉኛ ወረርሽኞችን ሁሉ አምጥቶባቸዋል።

😇 ኢትዮጵያን ከፍ የሚያደርጓት እነ ቅዱስ ያሬድ እየመጡ ነውና ተዋሕዷውያን ወደ አንድ እንሰባሰብ

💭 ሁሉም ከጸዳ በኋላ ቅዱስ ያሬድ በስውር እያሰለጠናቸው ያሉት ትክክለኛዎቹ ካህናት ይወጣሉ፤

እውነተኞቹን ተዋሕዶ ክርስቲያኖችን የሚሰበስብ፣ ክርስቶስን የሚወድና እስልምናን የሚጠላ አንድ ቅዱስ ሰው በእግዚአብሔር ተቀብቶ ይወጣል። ያኔ የእስልምና አምልኮ ከምድረ ገጽ ይጠፋል። እውነተኞቹ ኢትዮጵያን የሚያውቋት ያውቁታልና ወደ አንድ ይሰባሰባሉ። መቶ ሚሊየን የሚሆነው ነዋሪ ኢትዮጵያን አያውቃትምና ሁሉም ይጠፋል። በአፋቸው ሳይሆን በህሊናቸው ኢትዮጵያንና ተዋሕዶን ከልባቸው የያዙት፣ ደሞዝ እየተከፈላቸው ካህናት የሆኑት ሳይሆኑ፣ በደሞዙ የሚንጠራሩት ሳይሆኑ፣ በዘረኝነት የተለከፉት ሳይሆኑ፣ ዘረኛ፣ ዘማዊና ጉቦኛ ያልሆኑት፣ ዘረኛ ያልሆኑትንና በፍቅር የሚመላለሱትን ምዕመናንን ጨምሮ ሁሉም በቅዱሱ ሰው ዙሪያ ተሰባስበሰው ኢትዮጵያን ይኖሩባታል።

†††[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፲፩፥፮]†††

ተኵላ ከበግ ጠቦት ጋር ይቀመጣል፥ ነብርም ከፍየል ጠቦት ጋር ይተኛል፤ ጥጃና የአንበሳ ደቦል ፍሪዳም በአንድነት ያርፋሉ፤ ታናሽም ልጅ ይመራቸዋል።”

❖❖❖ይህ ዓለም ካዘጋጀልን ወጥመድና መከራ ሰውሮ ወደ አንድነት ይሰብስበን!❖❖❖

†††[ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፲፩]†††

ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፥ ከሥሩም ቍጥቋጥ ያፈራል።

የእግዚአብሔር መንፈስ፥ የጥበብና የማስተዋል መንፈስ፥ የምክርና የኃይል መንፈስ፥ የእውቀትና እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ ያርፍበታል።

እግዚአብሔርን በመፍራት ደስታውን ያያል። ዓይኑም እንደምታይ አይፈርድም፥ ጆሮውም እንደምትሰማ አይበይንም፤

ነገር ግን ለድሆች በጽድቅ ይፈርዳል፥ ለምድርም የዋሆች በቅንነት ይበይናል፤ በአፉም በትር ምድርን ይመታል፥ በከንፈሩም እስትንፋስ ክፉዎችን ይገድላል።

የወገቡ መታጠቂያ ጽድቅ፥ የጎኑም መቀነት ታማኝነት ይሆናል።

ተኵላ ከበግ ጠቦት ጋር ይቀመጣል፥ ነብርም ከፍየል ጠቦት ጋር ይተኛል፤ ጥጃና የአንበሳ ደቦል ፍሪዳም በአንድነት ያርፋሉ፤ ታናሽም ልጅ ይመራቸዋል።

ላምና ድብ አብረው ይሰማራሉ፥ ግልገሎቻቸውም በአንድነት ያርፋሉ፤ አንበሳም እንደ በሬ ገለባ ይበላል።

የሚጠባውም ሕፃን በእባብ ጕድጓድ ላይ ይጫወታል፥ ጡት የጣለውም ሕፃን በእፉኝት ቤት ላይ እጁን ይጭናል።

በተቀደሰው ተራራዬ ሁሉ ላይ አይጐዱም አያጠፉምም፤ ውኃ ባሕርን እንደሚከድን ምድር እግዚአብሔርን በማወቅ ትሞላለችና።

በዚያም ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ለአሕዛብ ምልክት ሊሆን የቆመውን የእሴይን ሥር አሕዛብ ይፈልጉታል፤ ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል።

፲፩ በዚያም ቀን እንዲህ ይሆናል፤ የቀረውን የሕዝቡን ቅሬታ ከአሦርና ከግብጽ፥ ከጳትሮስና ከኢትዮጵያ፥ ከኤላምና ከሰናዖር ከሐማትም፥ ከባሕርም ደሴቶች ይመልስ ዘንድ ጌታ እንደ ገና እጁን ይገልጣል።

፲፪ ለአሕዛብም ምልክትን ያቆማል፥ ከእስራኤልም የተጣሉትን ይሰበስባል፥ ከይሑዳም የተበተኑትን ከአራቱ የምድር ማዕዘኖች ያከማቻል።

፲፫ የኤፍሬምም ምቀኝነት ይርቃል፥ ይሑዳንም የሚያስጨንቁ ይጠፋሉ፤ ኤፍሬምም በይሑዳ አይቀናም፥ ይሑዳም ኤፍሬምን አያስጨንቅም።

፲፬ በምዕራብም በኩል በፍልስጥኤማውያን ጫንቃ ላይ እየበረሩ ይወርዳሉ፥ የምሥራቅንም ልጆች በአንድነት ይበዘብዛሉ፤ በኤዶምያስና በሞዓብም ላይ እጃቸውን ይዘረጋሉ፥ የአሞንም ልጆች ለእነርሱ ይታዘዛሉ።

፲፭ እግዚአብሔርም የግብጽን ባሕር ያጠፋል፤ በትኩሱም ነፋስ እጁን በወንዙ ላይ ያነሣል፥ ሰባት ፈሳሾችንም አድርጎ ይመታዋል፥ ሰዎችም በጫማቸው እንዲሻገሩ ያደርጋቸዋል።

፲፮ ከግብጽም በወጣ ጊዜ ለእስራኤል እንደ ነበረ፥ ለቀረው ለሕዝቡ ቅሬታ ከአሦር ጐዳና ይሆናል።

Saturday, May 9, 2026

The Birth of The Virgin Mary, Lideta LeMariam | ልደታ ለማርያም

https://www.bitchute.com/video/FuLGkBw3TgN7/

https://rumble.com/v79m9mk-the-birth-of-the-virgin-mary-lideta-lemariam-.html

♰ The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church celebrates the birth of the Virgin Mary, known as Lideta LeMariam (or Lideta), on Ginbot 1 (May 9 in the Gregorian calendar).

The feast commemorates her birth to Joachim and Anna—a birth believed to have marked the end of darkness and the beginning of salvation.

Key Aspects of the Celebration and Belief:

🧕 Significance: Mary's Birth is seen as the "star of the dawn" that heralded the coming of Jesus Christ, the Sun of Justice.

Parents: According to tradition, her parents, Joachim and Anna, were righteous but elderly and barren. They fasted and prayed for a child, promising to dedicate them to God, resulting in the birth of Mary.

Immaculate Conception: Ethiopian tradition considers Mary to be pure and holy from her conception, as she was born to bring forth the Incarnated Word, often viewed as being preserved from the original sin of Adam.

Celebration: The festival involves solemn church services, singing of "Lideta leMariam" hymns, and sometimes fasting beforehand. The birth is also commemorated on the 1st of every month in the Ethiopian calendar.

Location: While major celebrations happen throughout Ethiopia, Lalibela is a particularly significant site for this holiday.The Ethiopian Orthodox Church celebrates the Immaculate Conception of St. Mary by her mother Anna on Nehasie 7 (August 13), exactly nine months before her birth on Ginbot / May.

🧕 ከቅዱሳን ውስጥም ፍጥረት ሁሉ በንጽህና የማይተካከላት የብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት

😇 ከቅዱሳን ውስጥም ፍጥረት ሁሉ በንጽህና የማይተካከላት የብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷን ታሪክ ምእመናን ዘወትር ወር በገባ በመጀመሪያው ቀን "ልደታ" ብለው በመሰየም፣ በግንቦት ፩ ከዋዜማ አንስቶ በእለቱ በደማቅ ሥርዓት ከውጭ በመሆን ያከብሩታል፡፡ በዚህ ብቻ ሳይወሰኑ በሊባኖስ ተራራ የተፈጸመውን ድንቅ ተአምር በዝማሬ ያስቡታል፡፡ ከዝማሬ በተጨማሪም ሥዕሏን በመሣል እና አጠገባቸው አድርገው በመማጸን የእመቤታችን ልደትን ያከብራሉ፡፡

ቅዱሳት ሥዕላት ደግሞ የቅዱሳንን የሕይወት ጉዞና ተጋድሎ ፍንትው አድርገው በማሳየት ከቅዱሳን ጋር ኅብረት አንዲኖረን ያደርጋሉ፡፡ እኛም ከሁለት ሺ ዓመታት በፊት በሊባኖስ ተራራ የተፈጸመውን ታላቅ ተአምር በሥዕሉ አማካኝነት የደስታው ተካፋይ እንሆናለን፡፡ በመሆኑም የእመቤታችን ልደት ስናስብ ልቦናችን በተመስጦ ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሔድ እና መልካም ልደት እንድንላት ለውዷ እናታችን ከሥር ትውፊታቸውን የጠበቁ ሥዕሎች ቀርበዋል፡፡ በተጨማሪም በሥዕሏ ላይ የሚታዩ ዐብይት ጭብጦች በአጭሩ ተዘርዝረዋል፡፡

የእመቤታችን ልደታ ሥዕል በቤተ ክርስቲያን ሲሣል የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች ታሪክን በሚያጎላ መልኩ ይሣላል፡፡ ለምሳሌ ልጅ ባለመውለዳቸው ምክንያት አዝነው፣ ተኝተው ራእይ ሲመለከቱ እና እመቤታችን ተወልዳ ቅደስት ሐና አቅፋት ኢያቄም ደግሞ ሲመለከት ለብቻቸው ሆነው አሊያም ሌሎች ሰዎች የቅዱሳኑን ደስታ ለመካፈል በአካል መገኘታቸውን በሥዕል ይገለጣል፡፡

ከሥርም እነዚህን ታሪኮች የሚያብራሩ የብራና የግድግዳ እና የገበታ ጥንታዊ ሥዕሎች ቀርቧል፡፡ መልካም በዓል፡፡ እመቤታችን ከዚህ መቅሰፍት ትሰውረን ለቀጣይ ዐመትም በደስታ ከቁጥር ሳንጎደል "ልደትሽ ልደታችን ነው" ብለን አንድናመሰግናት እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

🧕 ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት | ምስጋና

❖❖❖ ልደታ ለማርያም፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ❖❖❖

❖❖❖በሰንበት ተማሪዎች የቀረበ ወረብ❖❖❖

የቅድስት ልደታ ለማርያም ክብረ በዓል ፩ ግንቦት ፪ሺ፱ ዓ.

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም "የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት" ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ “ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች” [ኢሳ ፯፡፲፬] ብሎ ትንቢት የተናገረላት ያቺ ድንግል በዚህች ዕለት ተወለደች፡፡ ይህች ቀን ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት " የወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።” [መዝ ፵፬፡፱] ብሎ የተናገረላት ንግሥት የተገኘችባት ዕለት ናት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ “ፀሐይን የተጎናጸፈች፣ ጨረቃን የተጫማች፣ አስራ ሁለት የክዋክብት አክሊል በራሷ ላይ ያላት።”[ራዕ ፲፪፡፩] ብሎ የመሰከረላት የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችባት ቀን ናት፡፡ የእርስዋም ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራዕይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን ሲገለጽ የነበረ ነው፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በነቢያት አንደበት

መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡ መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ [መዝ ፹፮፥፩፡፯]

እግዚአብሔር የዝማሬና የትንቢት ጸጋን ያበዛለት ክቡር ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥርወ ልደት አስቀድሞ በመንፈስ ቅዱስ መነጽርነት ተገልጾለት "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን /መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው/" በማለት ትንቢት ተናግሯል፡፡ "የተቀደሱ ተራሮች" ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ይህንን ትንቢትና እውነተኛውን የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ ቤተክርስቲያን "የእመቤታችን ማርያም ትውልዷ ባባቷ በኩል ከንጉሡ ከዳዊት ወገን ነው፤ በናቷም በኩል ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው፤ የአባቷ ስም ኢያቄም ነው፤ የእናቷም ስም ሐና ነው፡፡" ብላ ታስተምራለች፡፡

ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡ [ኢሳ. ፲፩፡፩]

ቁጥሩ ከዐበይት ነቢያት ወገን የሆነው ነብዩ ኢሳይያስም ጥበብንና እውቀትን በሚገልጽ ስለሚመጣውም ነገር ትንቢትን በሚያናግር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም ጽጌ (አበባ) የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት "ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ /ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል/" በማለት ታላቅ ትንቢትን ተናግሮ ነበር፡፡ ይህች በትርም ከእሴይ ዘር የተገኘችው በዚህች ዕለት ነውና ልደቷን በታላቅ ድምቀት እናከብራለን፡፡ ይህንን መሰረት በማድረግ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም "መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከእሴይ ሥር የተገኘሽ መዓዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ" በማለት በውዳሴ አመስግኗታል፡፡ "በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ” [መዝ.፻፴፩፡፲፫]" የተባለልን የአባቶቻችን ልጆች እኛም እንዲሁ እያልን እናመሰግናታለን፡፡

ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ፡ ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ፡፡ [መኃ ፬፡፰]

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ በሊባኖስ ስለመሆኑ አስቀድሞ ጠቢቡ ሰሎሞን "ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ ንዒ ወተወፅኢ እምቅድመ ሃይማኖት እምርእሰ ሳኔር ወኤርሞን አምግበበ አናብስት ወእምአድባረ አናምርት /ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔር ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች/" በማለት ተናግሮ ነበር፡፡ የዚህ ትንቢት ምስጢርም የእመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸው የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ ትንቢቱም ሲፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት ፩ ቀን በ፲፭ ዓ.ዓ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች፡፡

ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ የተባለው የነገረ ማርያም ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እመቤታችን በሊባኖስ እንደምትወለድ አስቀድሞ ሰሎሞን የተናገረው ቃልም መፈጸሙን ሲገልጽ "….የአናብስት ልጅ አልኩሽ፡፡ ሰሎሞን እንዲህ ሲል እንደተናገረ፡- ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሽ ነዪ፤ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው፡፡" በማለት አመስጥሮታል፡፡ እመቤታችንም በሊባኖስ ተራራ እንድትወለድ ምክንያት የሆነው በማሕፀን ሳለች የአርሳባንን ልጅ ዓይን በማብራቷና ሳሚናስ የሚባለውን የጦሊቅን ልጅ ከሞት በማስነሳቷ አይሁድ በቅናት ተነሳስተውባቸው ስለነበር ሐናና ኢያቄም ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሄዱ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ስለነገራቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌ

ከትንቢቱ በተጨማሪም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌም አስቀድሞ የተገለጸ ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል ከእርሷ ሰባት ትውልድ አስቀድሞ ለነበሩት ደጋግ ሰዎች እንዲሁም ለእናትና ለአባቷ የተገለጹት ምሳሌዎች በቅዱሳት መጻሕፍት በሰፊው ሰፍረው ይገኛሉ፡፡

ሰባተኛዪቱ እንቦሳ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋ ደግሞ ፀሓይን ስትወልድ አየሁ (ቴክታ)

በቅድስና የሚኖሩ ነገር ግን መካን የነበሩት ቴክታና ጴጥርቃ ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ ፤ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ስድስት ስትደርስ ፤ ስድስተኛዪቱ ጨረቃን ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሀገራቸው መፈክረ ሕልም (ሕልም ፈች ሊቅ) አለና ሂደው ነገሩት፡፡ ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ፤ ጨረቃይቱ ከፍጡራን በላይ የምትሆን ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡ የፀሐይ ነገር ግን አልተገለጸልኝም፤ እንደ ነብይ እንደ ንጉሥ ያለ ይሆናል አላቸው፡፡ እነርሱም ጊዜ ይተርጉመው ብለውት ሄዱ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጅ ወለዱ፡፡ ስሟንም "ረከብኩ ስእለትዬ፤ ረከብኩ ተምኔትዬ" /የተሳልኩትን አገኘሁ፤ የተመኘሁትን አገኘሁ/ ሲሉ "ሄኤሜን"አሏት፡፡ ሄኤሜን ዴርዴን፤ ዴርዴ ቶናን፤ ቶና ሲካርን፤ ሲካር ሄርሜላን፤ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡ ሐና ለአካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ ይሑዳ ለተወለደ ኢያቄም ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት፡፡ ከኢያቄምና ከሐናም በጨረቃ የተመሰለች ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡

ፀዓዳ ርግብ ሰባቱ ሰማያትን ሰንጥቃ መጥታ በማሕፀኔ ስታድር አየሁ (ቅድስት ሐና)

ኢያቄምና ሐና መካን ስለነበሩ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ጸልየው፤ ሲሰጣቸውም መልሰው ለእርሱ እንደሚሰጡ ስዕለትን ተስለው ነበር፡፡ ጸሎታቸው ሲደርስ ለሐና በሕልም ተገልጾላት ለባለቤቷ ለኢያቄም "ብእሴሃ አነኑ ርኢኩ በሕልምየ ርግብ ጸዐዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርእስየ ወቦአት ውስተ እዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርሥየ /ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብቶ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ፡፡" ብላዋለች፡፡ የዚህ ራእይ ምስጢርም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን፤ ፀዓዳ (ነጭ) መሆኗ ንጽሕናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ዘላለማዊ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ" ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን የምትፀንሰውን ንጽሕት ርግብ የተባለችውን እመቤታችንን የምትወልድ መሆኗን ሲያጠይቅ ነው።

ከሰባተኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ (ቅዱስ ኢያቄም)

በተመሳሳይ ኢያቄምም በሕልሙ ያየውን ለባለቤቱ ለሐና "እንዘ ይትረኀዉ ሰብዐቱ ሰማያት ዖፍ ጸዐዳ መጽአ ኀቤየ ወነበረ ዲበ ርእስየ /ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ" ብሎ በሕልሙ የተገለጸለትን ነግሯታል፡፡ የዚህም ራዕይ ምስጢር ዖፍ የተባለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባሕርዩ ነው፡፡ ኢያቄም "ከላይ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ" ማለቱ የኢያቄምን ባሕርይ ባሕርይ እንደሚያደርግ የሚያጠይቅ ሲሆን ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ባህርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩና መንግስቱ ናቸው።

የድንግል ማርያም ልደት በሐዲስ ኪዳን ሊቃውንት

የሐዲስ ኪዳን ሊቃውንትም ትንቢተ ነቢያትንና ወንጌልን በማጣጣም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት አመስጥረው አስተምረዋል፤ አመስግነዋል፤ ተቃኝተዋልም፡፡ የእርሷን ልደት እጅግ ብዙ ሊቃውንት በስፋትና በጥልቀት ያመሰጠሩት ሲሆን ለምሳሌ ያህል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡

ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች (ቅዱስ ያሬድ)

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ልደት "ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ/ ማርያምስ (ማርያም ግን) ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች፡፡" በማለት እርሷ በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና፣ በቅድስናና በድንግልና ስታበራ እንደነበርና ኋላም የዓለም ብርሃን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መውለዷን አመስጥሮ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም ስለ ሥርወ ልደቷ "እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕጹቂሃ…ሐረገ ወይን/ ሥሮቿ በምድር ጫፎቿም በሰማይ ያሉ…የወይን ሐረግ" በማለት የተወለደችው በምድር ከነበሩት ኢያቄምና ሐና መሆኑን የወለደችው ግን ሰማያዊውን ንጉሥ እንደሆነ በማመስጠር ዘምሯል፡፡ በዚህም ሰውና እግዚአብሔርን ያገናኘች መሰላል መሆኗል ገልጾ አስተምሯል፡፡

ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ (አባ ሕርያቆስ)

የብህንሳው ሊቀ ጳጳስ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም "ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ/ ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ" በማለት የድንግል ማርያም ጽንሰትና ልደት እንዴት እንደነበር በድርሰቱ አስፍሮታል፡፡ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚላት የሁላችን እናት ድንግል ማርያም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኋላ ግንቦት ፩ ቀን ተወልዳለች፡፡ እርስዋም ስትፀነስ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ከጥንተ አብሶ (original Sin) ጠብቋታል፤ አበሳው አልነካትም፡፡ ይህንንም ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በኃጢአት በተከበበ፣ መርገም በሞላበት ዓለም ውስጥ ከኃጢአት ከበደል ርቃ (ተለይታ) እንደ ጌዲዮን ጸምር በንጽህና የጠገኘች ንጽህት ዘር መሆኗን ሲያስረዳ "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር፡፡"[ኢሳ.፩፡፲፱]በማለት ተናግሯል፡፡ እንዲሁም ጠቢቡ ሰሎሞን ንጽህናዋን በትንቢት መነጽር አይቶ “ወዳጄ ሆይ፣ ሁለንተናሽ ውብ ነው፣ ምንም ነውር የለብሽም፡፡ ሙሽሪት ሆይ ከሊባኖስ ነዪ፡፡”[መሓልይ ፬፡፯፡፲፮] በማለት በንጽህና በቅድስና ያጌጠች፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያልነካት፣ የድህነታችን ምክንያት፣ የንጽህናችን መሰረት የሰው ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲዋሀድ ምክንያት የሆነች ንጽሕት የሰርግ ቤት ድንግል ማርያም በሊባኖስ የመወለዷን ነገር አስቀድሞ ነግሮናል፡፡

ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት (ቅዱስ እንድርያስ)

የቀርጤሱ ቅዱስ እንድርያስ የከበረ ስለሆነው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ታላቅነት "ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌው በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል፤ የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ ዕለት (ጌታ) መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነው፡፡” በማለት ገልጾታል፡፡ በእውነት የእርሷ ልደት የልዑል ማደሪያው መቅደስ የተሰራበት ዕለት ነውና ሁላችን እናከብረዋለን፡፡ በዚህም ዕለት "ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም/ እነሆ ዛሬ በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ" እያልን እንዘምራለን። ይህችን የልዑል ማደሪያ እናቷ ሐናና አባቷ ኢያቄምም በእጅጉ ተደስተው በተወለደች በስምንተኛ ቀኗ ስሟን "ማርያም" ብለው ሰይመዋታል፡፡

የእመቤታችን የልደት በዓል አከባበር

አባታችን አዳም በኃጢአት ከወደቀ በኋላ፣ ንስሃ በገባ ጊዜ አምላካችን ጌታ እግዚአብሔር የድህነት ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ቃል ኪዳኑም “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚል ነበር፡፡ ስለሆነም አዳም ፶፻፭፻/5500 ዘመን የሕይወት ምክንያት የሆነች የልጅ ልጁ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአብራኩ ከተከፈሉ ቅዱሳን ልጆቹ የምትወለድበትን ቀን ተስፋ እያደረገ ኖረ፡፡ የእመቤታችንን የድንግል ማርያምን የመወለዷን ዜና ተስፋ በማድረግ “ሴት” ይላት የነበረውን ሚስቱን ሔዋንን በእመቤታችን ምሳሌነት “ሔዋን”፣ የሕያዋን ሁሉ እናት ብሎ ሰየማት፡፡ [ዘፍ.፫፡፳] ዳግማዊ አዳም የተባለ ክርስቶስም የአዳምን ተስፋ በመስቀል ላይ በፈጸመ ጊዜ እውነተኛዋን ሔዋን (ዳግሚት፣ አማናዊት ሔዋንን) ድንግል ማርያምን በዮሐንስ ወንጌላዊ በኩል ለሕያዋን ምዕመናን ሁሉ እናት አድርጎ ሰጠ፡፡ [ዮሐ. ፲፱፡፳፮] ይህን የከበረ ምስጢር የማይረዳ “ክርስቲያን” እንዴት ያሳዝናል!? እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን የቀዳማዊ አባታችንን የአዳምን፣ እንዲሁም በዳግም ተፈጥሮ ያከበረንን ዳግማዊ አዳም የተባለ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ተቀብለን “የሕያዋን ሁሉ እናት” ድንግል ማርያምን ልደቷን በፍፁም ደስታ እናከብራለን፣ ከተወደደ ልጇ ምሕረትን ትለምንልን ዘንድም ወደ እርሷ እናንጋጥጣለን፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያለን ምዕመናን ከጌታችን ልደት ቀጥሎ በታላቅ ድምቀት የምናከብረው የልደት በዓል የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ነው፡፡ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ "በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።"[ሉቃ ፩፡፲፬] ከተባለ የድንግል ማርያም ልደት ምንኛ የሚያስደስት ይሆን?! የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት፣ የታየው ራዕይም በገሀድ የተከናወነበት፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ (ለሕያዋን ሁሉ) ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም በንጽህናዋ በቅድስናዋ ተደንቀው “እህትነ ነያ/እህታችን እነኋት” ብለው ያመሰግኗታል፡፡ በዘመናችን ያሉ የሰዎች ልደት በድምቀት የሚከበር ከሆነ ለሰው ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ምንኛ ሊከበር ይገባው ይሆን?! ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡ የሕይወት ክርስቶስ እናት ዛሬ ተወልዳለችና፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትዉፊት መሰረት ሐና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ፡፡ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ "ንፍሮና ጥራጥሬ" ነበር፡፡ይህንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ነገር ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መካከል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳዊ በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ (የእመቤታችን የልደት በዓል) ነዉ፡፡ በዚህ ዕለት አንዳንዶች ባለማወቅ ሌሎች ደግሞ በድፍረት "ለአድባር አዉጋር ነዉ፤ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ" እያሉ ለማያውቁት አምልኮ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቅቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ አሉ፡፡ እውነታው እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን እነዚህን የሃይማኖት ለዋጮች ሥራቸውን እንጸየፋለን፡፡ ስለሆነም ከእንደዚህ ዓይነቱ ባዕድ አምልኮ በመለየት ይህንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር ልናከብረው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ በምሕረቱ የጎበኘንን አምላካችንን ብቻ እያመለክን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን፡፡

Friday, April 10, 2026

✞ Crucifixion | On That Day, Children of Christ Became Christians & Children of the Antichrist Muslims

https://www.bitchute.com/video/5lkPo8oIrLVD/

https://rumble.com/v6s8bp9-crucifixion-on-that-day-children-of-christ-became-christians-and-children-o.html

የጌታችን ስቅለት | በዚያን ዕለት የከርስቶስ ልጆች ክርስቲያን፤ የክርስቶስ ተቃዋሚው ልጆች እስላም ተባሉ

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ "የድኅነት ቀን" ይባላል፡

፲፫ቱ ሕማማተ መስቀል

  • ፩ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)

  • ፪ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)

  • ፫ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይ መውደቅ)

  • ፬ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድ መረገጥ)

  • ፭ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋር መላተም)

  • ፮ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)

  • ፯ኛ. ተቀስፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)

  • ፰ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)

  • ፱ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)

  • ፲ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)

  • ፲፩ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)

  • ፲፪ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይ መሰቀል)

  • ፲፫ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትን መጠጣት)

ጌታችን ሲሰቅል የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል፤

  • . ፀሐይ ጨለመ፤

  • . ጨረቃ ደም ኾነ፤

  • . ከዋክብት ረገፉ፤

  • . የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ፤

  • . አለቶች ተፈረካከሱ፤

  • . መቃብራት ተከፈቱ፤

  • . ሙታን ተነሡ (ማቴ. ፳፯፥፶፩-፶፬)፡፡

ጌታችን በመስቀል ላይ ሳለ የሚከተሉትን ሰባት ዐበይት ቃላት አሰምቶ ተናግሯል፤

  • . "ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ (አምላኪየ አምላኪየ ለምን ተውኸኝ?)"

  • . "እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትኖራለህ"

  • . "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁትምና ይቅር በላቸው"

  • . እመቤታችንን "ሴትዮ ሆይ፣ እነሆ ልጅሽ" ደቀ መዝሙሩንም "እናትህ እነኋት" በማለት የቃል ኪዳን እናትነትና ልጅነት ማከናወኑ፤

  • . "አባት ሆይ በአንተ እጅ ነፍሴን አደራ እሰጣለሁ"

  • . "ተጠማሁ"

  • . "ዅሉ ተፈጸመ" (ማቴ. ፳፯፥፵፭-፵፮፤ ሉቃ. ፳፫፥፵፫-፵፮፤ ዮሐ. ፲፱፥፲-)፡፡

ከሰድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ጨለማ ኾኖ ከቈየ በኋላ ከዘጠኝ እስከ ማታ እንደ ተለመደው ብርሃን ሁኖአል፡፡ "ወፍና ሠርክ ይበርህ ብርሃነ ፀሐይ" እንዲል (ዘካ. ፲፬፥፯)፡፡ በዚህ ዕለት ሰባት መስተፃርራን (ጠበኞች) ታረቁ፤ ተስማሙ፡፡ እነዚህም፡- ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው (ኤፌ. ፪፥፲፤ ቈላ. ፩፥፳)፡፡ ጌታችን ጠዋት በሦስት ሰዓት ተገረፈ፤ በስድስት ሰዓት ተሰቀለ (ማቴ. ፳፯፥፩-፴፯፤ ሉቃ. ፳፫፥፩-፵፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፩)፡፡

ጌታችን በውኃው ተጠምቀን፣ ደሙን ተቀብለን የእግዚአብሔር ልጆች እንኾን ዘንድ ከቀኝ ጎድኑ ጥሩ ውኃ፣ ትኩስ ደም አፈሰሰልን (ዮሐ. ፲፱፥፴፬)፡፡ በዐሥራ አንድ ሰዓት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከመስቀል አውርደው ሽቶ እየረበረቡ በድርብ በፍታ ገንዘው ቀበሩት (ሉቃ. ፳፫፥፶-፶፬፤ ዮሐ. ፲፱፥፴፰-፵፪)፡፡ ነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዳ ነፍሳትን ነጻ አወጣች (፩ኛ ጴጥ. ፫፥፲፱)፡፡ በዚህ ጊዜ በርሃነ መለኮቱ በሲኦል ተገለጠ፡፡ ስለዚህም "ንሴብሖ ለእግዚአብሔር" እየተባለ ይዘመራል፡፡ ከሆሣዕና አንሥቶ ተከልክሎ የነበረው ኑዛዜ ይናዘዛል፤ ጸሎተ ፍትሐት ይደረጋል፡፡

ጌታም ቆላተ ዮሳፍጭ ከሚባል በረሀ አውርዶ መናውን ውሀውን ከወትሮ አብልጦ አወረደላቸውና ኃይሉን ከሂሎቱን አሳይቶ ወእንዘ ዓዲ መብልዖሙ ውስተ አፋሆሙ ነዘር እባብ አስንቶ ጐዳናቸውን እየስቀደደ አስፈጃቸው። ሙሴም አቤቱ ጌታዬ አሕዛብ ፳ኤልን የሚመግባቸው ቢያጣ ከበረሀ አውርዶ አስፈጃቸው እንዳይሉህ መድኃኒት ፈልግላቸው ብሎ ጸለየ። ጌታም የወዳጁን ጸሎት ፈጥኖ ይሰማልና ብርቱን እባብ አስመስለህ በተራራ ላይ ተራዳ ተክለህ ብርቱን በዚያ ላይ ሰቅለህ አሳያቸው ያን አይቶ ሰምቶ ያመነ ይዳን ያላመነ ይፈጸም አለው። ተራራው በቀራንዮ አምሳል ነው፤ ተራዳው የመስቀል ብርቱ የወልደ እግዚአብሔር እባብ የዲያብሎስ ቍስሉ የኃጢአት መርዙ የመርገመ ሥጋ የመርገመ ነፍስ በረኃው የገሃነም እሳት አምሳል ነው።

ያን አይተው ሰምተው ይዳኑ ማለት ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያመኑ ሐዋርያት፣ ሰምተው ያመኑ ምዕመናን የመዳናቸው አምሳል ነው። ያላመኑ ይፈጸሙ ማለቱ፡ ስቅለተ ክርስቶስን አይተው ያላመኑ አይሁድ ሰምተው ያላመኑ አይሁድ፣ ሰምተው ያላመኑ አሕዛብ ያለመዳናቸው አምሳል ነው።

ነፍስ ያለው እባብ የገደላቸውን ሰዎች ነፍስ የሌለው ብርት እንዳዳናቸው በባሕርዩ ሞት የሌለበት አምላክ ዲያብሎስ ያስገራቸውን ነፍሳት ተሰቅሎ ሞቶ የማዳኑ አምሳል ነው።

ጽዮን የተባለች ማኅፀነ ማርያም ደብረ መቅደሱ የተባለ አካሏ ነው

ጌታም እነዚያ አላወቁም እንጂ እኔስ በማኅፀነ ማርያም አድሬ ለጻድቃን ለሰማዕታት ነገሥሁላቸው በአይሁድ በመናፍቃን ነገሥሁባቸው ሲል ነው። አንድም ጽዮን የተባለ መሰቀሉ ደብረ መቅደሱ የተባለ አካሉ ነው

እነዚያ አላወቁም እንጂ እኔስ በመስቀል ተሰቅዬ ለጻድቃን ለሰማዕታት ነገሥሁላቸው በአይሁድ

በመናፍቃን ነገሥሁባቸው ሲል ነው እንዲህ ፯ት ተአምራት ሲሠሩ አይተው የባሕርይ አምላክ ነው እንጂ የባሕርይ አምላክማ ካልሆነ እንዲህ ያሉ ተአምራት ባልተሠሩ ነበር ያሉ ክርስቲያን ተባሉ።

አምላክ አይደለም፣ አልተወለደም፣ አልተሰቀለም፤ የአምላክ ወዳጅ ደግ ሰው ነብይ ብቻ እንጂ ያሉት እስላም ተባሉ። እስላምና ክርስቲያን የተባለበት ያን ዕለት ነው።

አይሁድ ግን አላክም ነብይም አይደለም ሐሳዌ መሲሕ ነው ከቄሣር በቀር ሌላ ንጉሥ የለም ብለው ካዱት።

መናፍቃን ካህናት አላውያን መኳንንት ከሀድያን ነገሥታት ሃይማኖታችሁን ጣሉ ፈጣሪያችሁን ካዱ ለጣኦት ስገዱ ብለው እንደ እኔ እራሳችሁን እየመቱ አክሊለ ሦክ ግንድ አሸክመው በብረት ቢቸነክሯችሁ መራር ሐሞት ቢያጠጧችሁ ዋጋችሁን በመንግሥት ተቀበሉት እንጂ ሃይማኖታችሁን አትጣሉ፤ ፈጣሪያችሁን አትካዱ፤ ለጣኦት አትስገዱ!በማለት ጌታችን አስተምሮናል።

ከፍኖተ መስቀሉ ከህያው ቅዱስ ቃሉ በረከት ይክፈለን

✞ Today millions of Orthodox Christians commemorate Good Friday, also known as “Great Friday” to remember the events leading up to Jesus' Crucifixion.

In Ethiopia, Good Friday is known locally as Siklet which translates to Crucifixion of the Lord Jesus Christ. It is a day of fasting, intense prayer and prostrations.

Followers of Ethiopian Orthodox Churches share the religious tradition with other Orthodox Churches. In Ethiopia, churches outside the Ethiopian Orthodox Church including Catholic celebrate the good Friday along with the Ethiopian Church.

Good Friday is the holiday that Lord and Savior Jesus Christ was crucified for the salvation of human race. He was beaten hard, spited on and dragged with a robe all the way through to Calvary.

After His capture betrayed by Judas on Thursday eve subsequent to His prayer in Gethsemane, the Jews took Him and started their torture. Early morning on this Holy Friday, Lord Jesus Christ was brought to trial in front of the Jewish leader Pilate. Convicted for a crime He did not commit, Lord Jesus was tortured and tormented until He reached to the Calvary for crucifixion. Upon it was revealed miracles including the darkening of the sun, the bleeding of the moon and the falling of the stars whilst Lord Jesus Christ separated His divine soul from His body at the ninth hour. Then after, Joseph and Nicodimus took His holy body and buried it.

✞ A chapter in one of the Prayer books (The Passion of Cross or Himamat Meskel) of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church teaches us the following very important lesson:

“They did not know, but I was crucified and reigned over the righteous and the martyrs, so the Jews who saw those 7 miracles being done, were called Christians because they said that it could only be a God of nature who is showing us these miracles, and if He was not a God of nature, such miracles would not have been done.„

And,

☪ “Those who deny the divinity of Jesus by saying, „He is not God, He was not born, He is not The Son of God, God doesn't have a son, He was not crucified, He is only a friend of God, a good man and just a prophet; They are called Muslims, or followers of Islam. It was on that very day that Islam and Christianity were called as such.”

May God accept our prayer, fasting and all our endeavors on the great lent and redeem us; Amen!

The Good Friday procession of the Ethiopian Orthodox Church in Jerusalem | ስቅለት በኢየሩሳሌም

https://www.bitchute.com/video/HwTCCb7lHHqN/

ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡

Dr. Fauci is A Liar: Tulsi Gabbard Releases Evidence Against Italo-American Fauci

https://www.bitchute.com/video/iX7lwMS8RhcX/ https://rumble.com/v7bjjvs-dr.-fauci-is-a-liar-tulsi-gabbard-releases-evidence-against-italo-am...