Showing posts with label ቅድስት ማርያም. Show all posts
Showing posts with label ቅድስት ማርያም. Show all posts

Saturday, May 9, 2026

The Birth of The Virgin Mary, Lideta LeMariam | ልደታ ለማርያም

https://www.bitchute.com/video/FuLGkBw3TgN7/

https://rumble.com/v79m9mk-the-birth-of-the-virgin-mary-lideta-lemariam-.html

♰ The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church celebrates the birth of the Virgin Mary, known as Lideta LeMariam (or Lideta), on Ginbot 1 (May 9 in the Gregorian calendar).

The feast commemorates her birth to Joachim and Anna—a birth believed to have marked the end of darkness and the beginning of salvation.

Key Aspects of the Celebration and Belief:

🧕 Significance: Mary's Birth is seen as the "star of the dawn" that heralded the coming of Jesus Christ, the Sun of Justice.

Parents: According to tradition, her parents, Joachim and Anna, were righteous but elderly and barren. They fasted and prayed for a child, promising to dedicate them to God, resulting in the birth of Mary.

Immaculate Conception: Ethiopian tradition considers Mary to be pure and holy from her conception, as she was born to bring forth the Incarnated Word, often viewed as being preserved from the original sin of Adam.

Celebration: The festival involves solemn church services, singing of "Lideta leMariam" hymns, and sometimes fasting beforehand. The birth is also commemorated on the 1st of every month in the Ethiopian calendar.

Location: While major celebrations happen throughout Ethiopia, Lalibela is a particularly significant site for this holiday.The Ethiopian Orthodox Church celebrates the Immaculate Conception of St. Mary by her mother Anna on Nehasie 7 (August 13), exactly nine months before her birth on Ginbot / May.

🧕 ከቅዱሳን ውስጥም ፍጥረት ሁሉ በንጽህና የማይተካከላት የብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት

😇 ከቅዱሳን ውስጥም ፍጥረት ሁሉ በንጽህና የማይተካከላት የብፅዕት ቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷን ታሪክ ምእመናን ዘወትር ወር በገባ በመጀመሪያው ቀን "ልደታ" ብለው በመሰየም፣ በግንቦት ፩ ከዋዜማ አንስቶ በእለቱ በደማቅ ሥርዓት ከውጭ በመሆን ያከብሩታል፡፡ በዚህ ብቻ ሳይወሰኑ በሊባኖስ ተራራ የተፈጸመውን ድንቅ ተአምር በዝማሬ ያስቡታል፡፡ ከዝማሬ በተጨማሪም ሥዕሏን በመሣል እና አጠገባቸው አድርገው በመማጸን የእመቤታችን ልደትን ያከብራሉ፡፡

ቅዱሳት ሥዕላት ደግሞ የቅዱሳንን የሕይወት ጉዞና ተጋድሎ ፍንትው አድርገው በማሳየት ከቅዱሳን ጋር ኅብረት አንዲኖረን ያደርጋሉ፡፡ እኛም ከሁለት ሺ ዓመታት በፊት በሊባኖስ ተራራ የተፈጸመውን ታላቅ ተአምር በሥዕሉ አማካኝነት የደስታው ተካፋይ እንሆናለን፡፡ በመሆኑም የእመቤታችን ልደት ስናስብ ልቦናችን በተመስጦ ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሔድ እና መልካም ልደት እንድንላት ለውዷ እናታችን ከሥር ትውፊታቸውን የጠበቁ ሥዕሎች ቀርበዋል፡፡ በተጨማሪም በሥዕሏ ላይ የሚታዩ ዐብይት ጭብጦች በአጭሩ ተዘርዝረዋል፡፡

የእመቤታችን ልደታ ሥዕል በቤተ ክርስቲያን ሲሣል የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች ታሪክን በሚያጎላ መልኩ ይሣላል፡፡ ለምሳሌ ልጅ ባለመውለዳቸው ምክንያት አዝነው፣ ተኝተው ራእይ ሲመለከቱ እና እመቤታችን ተወልዳ ቅደስት ሐና አቅፋት ኢያቄም ደግሞ ሲመለከት ለብቻቸው ሆነው አሊያም ሌሎች ሰዎች የቅዱሳኑን ደስታ ለመካፈል በአካል መገኘታቸውን በሥዕል ይገለጣል፡፡

ከሥርም እነዚህን ታሪኮች የሚያብራሩ የብራና የግድግዳ እና የገበታ ጥንታዊ ሥዕሎች ቀርቧል፡፡ መልካም በዓል፡፡ እመቤታችን ከዚህ መቅሰፍት ትሰውረን ለቀጣይ ዐመትም በደስታ ከቁጥር ሳንጎደል "ልደትሽ ልደታችን ነው" ብለን አንድናመሰግናት እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

🧕 ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት | ምስጋና

❖❖❖ ልደታ ለማርያም፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ❖❖❖

❖❖❖በሰንበት ተማሪዎች የቀረበ ወረብ❖❖❖

የቅድስት ልደታ ለማርያም ክብረ በዓል ፩ ግንቦት ፪ሺ፱ ዓ.

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም "የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት" ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ “ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች” [ኢሳ ፯፡፲፬] ብሎ ትንቢት የተናገረላት ያቺ ድንግል በዚህች ዕለት ተወለደች፡፡ ይህች ቀን ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት " የወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።” [መዝ ፵፬፡፱] ብሎ የተናገረላት ንግሥት የተገኘችባት ዕለት ናት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ “ፀሐይን የተጎናጸፈች፣ ጨረቃን የተጫማች፣ አስራ ሁለት የክዋክብት አክሊል በራሷ ላይ ያላት።”[ራዕ ፲፪፡፩] ብሎ የመሰከረላት የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችባት ቀን ናት፡፡ የእርስዋም ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራዕይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን ሲገለጽ የነበረ ነው፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በነቢያት አንደበት

መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፡ መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው፡፡ [መዝ ፹፮፥፩፡፯]

እግዚአብሔር የዝማሬና የትንቢት ጸጋን ያበዛለት ክቡር ዳዊት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥርወ ልደት አስቀድሞ በመንፈስ ቅዱስ መነጽርነት ተገልጾለት "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን /መሠረቶችዋ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው/" በማለት ትንቢት ተናግሯል፡፡ "የተቀደሱ ተራሮች" ያለውም የእመቤታችን ሥርወ ልደት ከቤተ መንግሥትና ከቤተ ክህነት ከሆኑት ከተቀደሱት ከኢያቄምና ከሐና የመሆኑን ነገር ሲያመለክት ነው፡፡ ይህንን ትንቢትና እውነተኛውን የእመቤታችንን የትውልድ ሀረግ አስማምታ ቤተክርስቲያን "የእመቤታችን ማርያም ትውልዷ ባባቷ በኩል ከንጉሡ ከዳዊት ወገን ነው፤ በናቷም በኩል ከካህኑ ከአሮን ወገን ነው፤ የአባቷ ስም ኢያቄም ነው፤ የእናቷም ስም ሐና ነው፡፡" ብላ ታስተምራለች፡፡

ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ፡ ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል፡፡ [ኢሳ. ፲፩፡፩]

ቁጥሩ ከዐበይት ነቢያት ወገን የሆነው ነብዩ ኢሳይያስም ጥበብንና እውቀትን በሚገልጽ ስለሚመጣውም ነገር ትንቢትን በሚያናግር በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ከነገደ ዕሴይ እንደሚሆንና እርሷም ጽጌ (አበባ) የተባለ አካላዊ ቃል ክርስቶስን በሕቱም ድንግልና እንደምትወልድ ተገልጾለት "ትወፅእ በትር እምሥርወ ዕሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ /ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች፤ አበባም ከእርሷ ይወጣል/" በማለት ታላቅ ትንቢትን ተናግሮ ነበር፡፡ ይህች በትርም ከእሴይ ዘር የተገኘችው በዚህች ዕለት ነውና ልደቷን በታላቅ ድምቀት እናከብራለን፡፡ ይህንን መሰረት በማድረግ ሊቁ ቅዱስ ኤፍሬም "መልካሟ ርግብ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፤ ከእሴይ ሥር የተገኘሽ መዓዛሽ ያማረ አበባ አንቺ ነሽ" በማለት በውዳሴ አመስግኗታል፡፡ "በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ” [መዝ.፻፴፩፡፲፫]" የተባለልን የአባቶቻችን ልጆች እኛም እንዲሁ እያልን እናመሰግናታለን፡፡

ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ፡ ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ፡፡ [መኃ ፬፡፰]

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ በሊባኖስ ስለመሆኑ አስቀድሞ ጠቢቡ ሰሎሞን "ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ ንዒ ወተወፅኢ እምቅድመ ሃይማኖት እምርእሰ ሳኔር ወኤርሞን አምግበበ አናብስት ወእምአድባረ አናምርት /ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ ከአማና ራስ ከሳኔር ከኤርሞን ራስ ከአንበሶች መኖሪያ ከነብሮችም ተራራ ተመልከች/" በማለት ተናግሮ ነበር፡፡ የዚህ ትንቢት ምስጢርም የእመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸው የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ ትንቢቱም ሲፈጸም ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት ፩ ቀን በ፲፭ ዓ.ዓ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች፡፡

ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ የተባለው የነገረ ማርያም ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እመቤታችን በሊባኖስ እንደምትወለድ አስቀድሞ ሰሎሞን የተናገረው ቃልም መፈጸሙን ሲገልጽ "….የአናብስት ልጅ አልኩሽ፡፡ ሰሎሞን እንዲህ ሲል እንደተናገረ፡- ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሽ ነዪ፤ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው፡፡" በማለት አመስጥሮታል፡፡ እመቤታችንም በሊባኖስ ተራራ እንድትወለድ ምክንያት የሆነው በማሕፀን ሳለች የአርሳባንን ልጅ ዓይን በማብራቷና ሳሚናስ የሚባለውን የጦሊቅን ልጅ ከሞት በማስነሳቷ አይሁድ በቅናት ተነሳስተውባቸው ስለነበር ሐናና ኢያቄም ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሄዱ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ስለነገራቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡

የድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌ

ከትንቢቱ በተጨማሪም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በራዕይና በምሳሌም አስቀድሞ የተገለጸ ነበር፡፡ ከእነዚህም መካከል ከእርሷ ሰባት ትውልድ አስቀድሞ ለነበሩት ደጋግ ሰዎች እንዲሁም ለእናትና ለአባቷ የተገለጹት ምሳሌዎች በቅዱሳት መጻሕፍት በሰፊው ሰፍረው ይገኛሉ፡፡

ሰባተኛዪቱ እንቦሳ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃዋ ደግሞ ፀሓይን ስትወልድ አየሁ (ቴክታ)

በቅድስና የሚኖሩ ነገር ግን መካን የነበሩት ቴክታና ጴጥርቃ ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ ፤ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ስድስት ስትደርስ ፤ ስድስተኛዪቱ ጨረቃን ጨረቃዋም ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሀገራቸው መፈክረ ሕልም (ሕልም ፈች ሊቅ) አለና ሂደው ነገሩት፡፡ ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ፤ ጨረቃይቱ ከፍጡራን በላይ የምትሆን ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡ የፀሐይ ነገር ግን አልተገለጸልኝም፤ እንደ ነብይ እንደ ንጉሥ ያለ ይሆናል አላቸው፡፡ እነርሱም ጊዜ ይተርጉመው ብለውት ሄዱ፡፡ ከዚህ በኋላ ልጅ ወለዱ፡፡ ስሟንም "ረከብኩ ስእለትዬ፤ ረከብኩ ተምኔትዬ" /የተሳልኩትን አገኘሁ፤ የተመኘሁትን አገኘሁ/ ሲሉ "ሄኤሜን"አሏት፡፡ ሄኤሜን ዴርዴን፤ ዴርዴ ቶናን፤ ቶና ሲካርን፤ ሲካር ሄርሜላን፤ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡ ሐና ለአካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ ይሑዳ ለተወለደ ኢያቄም ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት፡፡ ከኢያቄምና ከሐናም በጨረቃ የተመሰለች ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡

ፀዓዳ ርግብ ሰባቱ ሰማያትን ሰንጥቃ መጥታ በማሕፀኔ ስታድር አየሁ (ቅድስት ሐና)

ኢያቄምና ሐና መካን ስለነበሩ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ጸልየው፤ ሲሰጣቸውም መልሰው ለእርሱ እንደሚሰጡ ስዕለትን ተስለው ነበር፡፡ ጸሎታቸው ሲደርስ ለሐና በሕልም ተገልጾላት ለባለቤቷ ለኢያቄም "ብእሴሃ አነኑ ርኢኩ በሕልምየ ርግብ ጸዐዳ መጽአት ኀቤየ ወነበረት ዲበ ርእስየ ወቦአት ውስተ እዝንየ ወኀደረት ውስተ ከርሥየ /ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብቶ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ፡፡" ብላዋለች፡፡ የዚህ ራእይ ምስጢርም ርግብ የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትሆን፤ ፀዓዳ (ነጭ) መሆኗ ንጽሕናዋ፣ ቅድስናዋ፣ ዘላለማዊ ድንግልናዋ ነው፡፡ ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ተቀምጣ ከራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማሕፀኔ ስትተኛ አየሁ" ማለቷ ብሥራተ ገብርኤልን በጆሮዋ ሰምታ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን የምትፀንሰውን ንጽሕት ርግብ የተባለችውን እመቤታችንን የምትወልድ መሆኗን ሲያጠይቅ ነው።

ከሰባተኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ (ቅዱስ ኢያቄም)

በተመሳሳይ ኢያቄምም በሕልሙ ያየውን ለባለቤቱ ለሐና "እንዘ ይትረኀዉ ሰብዐቱ ሰማያት ዖፍ ጸዐዳ መጽአ ኀቤየ ወነበረ ዲበ ርእስየ /ሰባቱ ሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ዖፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ" ብሎ በሕልሙ የተገለጸለትን ነግሯታል፡፡ የዚህም ራዕይ ምስጢር ዖፍ የተባለው አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ነጭነቱ ንጽሐ ባሕርዩ ነው፡፡ ኢያቄም "ከላይ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ" ማለቱ የኢያቄምን ባሕርይ ባሕርይ እንደሚያደርግ የሚያጠይቅ ሲሆን ሰባቱ ሰማያት የተባሉ የጌታችን ልዩ ባህርይው፣ ምልአቱ፣ ስፍሃቱ፣ ርቀቱ፣ ልእልናው፣ ዕበዩና መንግስቱ ናቸው።

የድንግል ማርያም ልደት በሐዲስ ኪዳን ሊቃውንት

የሐዲስ ኪዳን ሊቃውንትም ትንቢተ ነቢያትንና ወንጌልን በማጣጣም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት አመስጥረው አስተምረዋል፤ አመስግነዋል፤ ተቃኝተዋልም፡፡ የእርሷን ልደት እጅግ ብዙ ሊቃውንት በስፋትና በጥልቀት ያመሰጠሩት ሲሆን ለምሳሌ ያህል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡

ማርያምስ ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች (ቅዱስ ያሬድ)

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ልደት "ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ/ ማርያምስ (ማርያም ግን) ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች፡፡" በማለት እርሷ በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና፣ በቅድስናና በድንግልና ስታበራ እንደነበርና ኋላም የዓለም ብርሃን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መውለዷን አመስጥሮ ተናግሯል፡፡ በተጨማሪም ስለ ሥርወ ልደቷ "እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕጹቂሃ…ሐረገ ወይን/ ሥሮቿ በምድር ጫፎቿም በሰማይ ያሉ…የወይን ሐረግ" በማለት የተወለደችው በምድር ከነበሩት ኢያቄምና ሐና መሆኑን የወለደችው ግን ሰማያዊውን ንጉሥ እንደሆነ በማመስጠር ዘምሯል፡፡ በዚህም ሰውና እግዚአብሔርን ያገናኘች መሰላል መሆኗል ገልጾ አስተምሯል፡፡

ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ (አባ ሕርያቆስ)

የብህንሳው ሊቀ ጳጳስ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም "ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ/ ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም፤ በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ" በማለት የድንግል ማርያም ጽንሰትና ልደት እንዴት እንደነበር በድርሰቱ አስፍሮታል፡፡ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚላት የሁላችን እናት ድንግል ማርያም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐናና ከኢያቄም ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ከዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በኋላ ግንቦት ፩ ቀን ተወልዳለች፡፡ እርስዋም ስትፀነስ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ከጥንተ አብሶ (original Sin) ጠብቋታል፤ አበሳው አልነካትም፡፡ ይህንንም ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በኃጢአት በተከበበ፣ መርገም በሞላበት ዓለም ውስጥ ከኃጢአት ከበደል ርቃ (ተለይታ) እንደ ጌዲዮን ጸምር በንጽህና የጠገኘች ንጽህት ዘር መሆኗን ሲያስረዳ "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር፡፡"[ኢሳ.፩፡፲፱]በማለት ተናግሯል፡፡ እንዲሁም ጠቢቡ ሰሎሞን ንጽህናዋን በትንቢት መነጽር አይቶ “ወዳጄ ሆይ፣ ሁለንተናሽ ውብ ነው፣ ምንም ነውር የለብሽም፡፡ ሙሽሪት ሆይ ከሊባኖስ ነዪ፡፡”[መሓልይ ፬፡፯፡፲፮] በማለት በንጽህና በቅድስና ያጌጠች፣ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ያልነካት፣ የድህነታችን ምክንያት፣ የንጽህናችን መሰረት የሰው ባህርይ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲዋሀድ ምክንያት የሆነች ንጽሕት የሰርግ ቤት ድንግል ማርያም በሊባኖስ የመወለዷን ነገር አስቀድሞ ነግሮናል፡፡

ይህች ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀባት ዕለት ናት (ቅዱስ እንድርያስ)

የቀርጤሱ ቅዱስ እንድርያስ የከበረ ስለሆነው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት ታላቅነት "ይህ በዓል በሐዲስና በብሉይ ኪዳን መካከል መገኛ ሆነ፡፡ ምሳሌዎቹ በእዉነታ፣ አሮጌው በአዲስ ቃል ኪዳን ተተኩ፡፡ ፍጥረት ሁሉ በደስታ ይዘምራል፤ የዚህን ቀንም ደስታ ይካፈላል፡፡ ይህ ዕለት (ጌታ) መቅደሱን የሰራበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ትልቅ ሕንፃ የታነጸበትና ፍጡር የፈጣሪ ማደሪያ ለመሆን የተዘጋጀበት ዕለት ነው፡፡” በማለት ገልጾታል፡፡ በእውነት የእርሷ ልደት የልዑል ማደሪያው መቅደስ የተሰራበት ዕለት ነውና ሁላችን እናከብረዋለን፡፡ በዚህም ዕለት "ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም/ እነሆ ዛሬ በእመቤታችን ልደት ደስታ ሆነ" እያልን እንዘምራለን። ይህችን የልዑል ማደሪያ እናቷ ሐናና አባቷ ኢያቄምም በእጅጉ ተደስተው በተወለደች በስምንተኛ ቀኗ ስሟን "ማርያም" ብለው ሰይመዋታል፡፡

የእመቤታችን የልደት በዓል አከባበር

አባታችን አዳም በኃጢአት ከወደቀ በኋላ፣ ንስሃ በገባ ጊዜ አምላካችን ጌታ እግዚአብሔር የድህነት ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ቃል ኪዳኑም “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚል ነበር፡፡ ስለሆነም አዳም ፶፻፭፻/5500 ዘመን የሕይወት ምክንያት የሆነች የልጅ ልጁ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከአብራኩ ከተከፈሉ ቅዱሳን ልጆቹ የምትወለድበትን ቀን ተስፋ እያደረገ ኖረ፡፡ የእመቤታችንን የድንግል ማርያምን የመወለዷን ዜና ተስፋ በማድረግ “ሴት” ይላት የነበረውን ሚስቱን ሔዋንን በእመቤታችን ምሳሌነት “ሔዋን”፣ የሕያዋን ሁሉ እናት ብሎ ሰየማት፡፡ [ዘፍ.፫፡፳] ዳግማዊ አዳም የተባለ ክርስቶስም የአዳምን ተስፋ በመስቀል ላይ በፈጸመ ጊዜ እውነተኛዋን ሔዋን (ዳግሚት፣ አማናዊት ሔዋንን) ድንግል ማርያምን በዮሐንስ ወንጌላዊ በኩል ለሕያዋን ምዕመናን ሁሉ እናት አድርጎ ሰጠ፡፡ [ዮሐ. ፲፱፡፳፮] ይህን የከበረ ምስጢር የማይረዳ “ክርስቲያን” እንዴት ያሳዝናል!? እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን የቀዳማዊ አባታችንን የአዳምን፣ እንዲሁም በዳግም ተፈጥሮ ያከበረንን ዳግማዊ አዳም የተባለ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል ተቀብለን “የሕያዋን ሁሉ እናት” ድንግል ማርያምን ልደቷን በፍፁም ደስታ እናከብራለን፣ ከተወደደ ልጇ ምሕረትን ትለምንልን ዘንድም ወደ እርሷ እናንጋጥጣለን፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያለን ምዕመናን ከጌታችን ልደት ቀጥሎ በታላቅ ድምቀት የምናከብረው የልደት በዓል የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ነው፡፡ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ "በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።"[ሉቃ ፩፡፲፬] ከተባለ የድንግል ማርያም ልደት ምንኛ የሚያስደስት ይሆን?! የነቢያቱ ትንቢት የተፈፀመበት፣ የታየው ራዕይም በገሀድ የተከናወነበት፣ የብሉይ ኪዳን ማብቂያ የሐዲስ ኪዳን መጀመሪያ ናትና ልደቷ ለሰው ልጆች ሁሉ (ለሕያዋን ሁሉ) ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡ ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትም በንጽህናዋ በቅድስናዋ ተደንቀው “እህትነ ነያ/እህታችን እነኋት” ብለው ያመሰግኗታል፡፡ በዘመናችን ያሉ የሰዎች ልደት በድምቀት የሚከበር ከሆነ ለሰው ልጅ መዳን ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት የተወለደችበት ቀን ምንኛ ሊከበር ይገባው ይሆን?! ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ከዚህ ታላቅ በዓል በረከት ረድኤትን እንድናገኝበት ነው፡፡ የሕይወት ክርስቶስ እናት ዛሬ ተወልዳለችና፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትዉፊት መሰረት ሐና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ፡፡ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ "ንፍሮና ጥራጥሬ" ነበር፡፡ይህንን ትዉፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ነገር ግን በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መካከል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳዊ በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ (የእመቤታችን የልደት በዓል) ነዉ፡፡ በዚህ ዕለት አንዳንዶች ባለማወቅ ሌሎች ደግሞ በድፍረት "ለአድባር አዉጋር ነዉ፤ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ" እያሉ ለማያውቁት አምልኮ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቅቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ አሉ፡፡ እውነታው እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን እነዚህን የሃይማኖት ለዋጮች ሥራቸውን እንጸየፋለን፡፡ ስለሆነም ከእንደዚህ ዓይነቱ ባዕድ አምልኮ በመለየት ይህንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር ልናከብረው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ በምሕረቱ የጎበኘንን አምላካችንን ብቻ እያመለክን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡

አምላካችን እግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን፡፡

Monday, December 1, 2025

Giant Hole on Sun That Can Fit 14 Earths Could Explode Anytime | Bye! Bye! Internet?

https://rumble.com/v72gsny-giant-hole-on-sun-that-can-fit-14-earths-could-explode-anytime-bye-bye-inte.html

https://www.bitchute.com/video/IXlf5aPbKPHg/

ገብርኤል 🧕 ማርያም 😇 ኡራኤል ጊዮርጊስ ተክለ ሐይማኖት ❖ መርቆርዮስ ዮሴፍ መድኃኔ ዓለም

🌞 በፀሐይ ላይ ያለው ግዙፍ ቀዳዳ በማንኛውም ጊዜ ሊፈነዳ ይችላል | ባይ! ባይ! በይነመረብ/ኢንተርነት + ሳተላይት + ጂ ፒ ኤስ + ድሮን?

ፀሐይ ባለፉት ዓመታት ውስጥ ግዙፍ የኢትዮጵያ ካርታ-መሰል የጨለማ ክበቦችን እየለበሰች ነው። አብረው፣ እነዚህ ጨለማ ክበቦች ከምድር መጠን አስራ አራት/14 እጥፍ ያህል አካባቢ ይሸፍናሉ።

በማንኛውም ጊዜ ሊፈነዱም ይችላሉ።

🧕 ቅድስት ማርያም የጽዮን ልጅ ናት = “ፀሐይን የተጐናጸፈች” ሴት = የቃል ኪዳኑ ታቦት

[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፩፲፱ ]❖

በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት በመቅደሱ ታየ፥ መብረቅና ድምፅም ነጐድጓድም የምድርም መናወጥ ታላቅም በረዶ ሆነ።“

[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፪፥፩]❖

ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”

🧕 ማርያምና የቃል ኪዳኑ ታቦት በእግዚአብሔር መንፈስ “ተጸለሉ/ተሸፈኑ።”

[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፩፴፭ ]❖

መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት። መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።”

😇 ኡራኤል ማለት ትርጉሙ “የብርሃን ጌታ”፣ ”የአምላክ ብርሃን" ማለት ነው

😇 ቅዱስ ኡራኤል | መጽሐፈ ሔኖክ፤ የሊቀ መላእክት በቀል በአዛዝኤልና ጭፍሮቹ ላይ

🌞 The Sun is covered in dark patches bigger than Earth. A powerful flare has already erupted, with more likely coming.

The Sun is wearing some of its largest dark circles in years. Together, these dark circles cover an area almost 14 times the size of Earth.

They could burst at any point of time.

🌞 Giant New Sunspot and X-Class Solar Flare Could Bring Bright Auroras

https://www.forbes.com/sites/jamiecartereurope/2025/12/01/giant-new-sunspot-and-x-class-solar-flare-could-bring-bright-auroras/

A spot on the sun 10 times larger than Earth has been seen on the solar surface — and its appearance coincided with a massive solar flare.

This is the most complex sun spot region we have seen this cycle and in quite a while. It is showing some serious complexity and will be earth facing over the next 12 days. Would you fly?

Sunspots are areas of intense and complex magnetic fields that produce solar eruptions, according to NASA. Earth-orbiting satellites detected an X1.9 class solar flare at 02:49 UTC on Dec. 1, 2025. It came in the wake of a couple of weaker M-class solar flares.

Massive Sunspot

The massive sunspot, dubbed AR 4294-96, is one of the biggest seen in a decade and expected to be the source of solar flares over the next few weeks, but Dec. 1's solar flare actually came from a smaller one called AR 4295, according to SpaceWeather.com.

Solar flares alone do not cause displays of aurora at Earth. Large solar X-ray flares can change Earth’s ionosphere, causing radio blackouts on the day-side of the Earth, according to NOAA. This one saw a blackout in Australia.

The electromagnetic radiation from a solar flare travels at the speed of light, taking just eight minutes to reach Earth. It’s what can follow in the aftermath of a big solar flare — a coronal mass ejection — that can lead to geomagnetic storms. That’s when an aurora can develop.

🧕 St. Mary is The Daughter of Zion = The Woman “Clothed with THE SUN” = The Ark of The Covenant

🧕 The Mother God, St. Mary, the New Ark of the Covenant

In the Book of Revelation (11:19) the Ark of the Covenant appears again, this time in the Celestial Temple in fulfillment of the prophecy of Jeremiah. This vision of The Ark leads immediately in revelation to the vision of the woman clothed with THE SUN who was with child (rev. 12:1). The image is that of Mary, presented as Mother of the Messiah and spiritual Mother of Israel, the New Ark of the Covenant.

🧕 Mary as the Ark of the New Covenant – Revelation

Rev: 11:19 “19 Then the sanctuary of God in heaven opened, and the ark of the covenant could be seen inside it. Then came flashes of lightning, peals of thunder and an earthquake and violent hail.”

Immediately following this verse we read of the “woman, robed with the sun, standing on the moon, and on her head a crown of TWELVE/ 12 stars”. The Ark of the Covenant as we have seen above, is none other than Mary, Jesus’ mother, so Mary is the woman spoken of here. (Remember that chapter numbers were only added to the bible in the twelth century, and verse numbers in the sixteenth century.)

Rev: 12:1 “1 Now a great sign appeared in heaven: a woman, robed with the sun, standing on the moon, and on her head a crown of twelve stars.

Rev 12: 4-5 “4 Its tail swept a third of the stars from the sky and hurled them to the ground, and the dragon stopped in front of the woman as she was at the point of giving birth, so that it could eat the child as soon as it was born.

5 The woman was delivered of a boy, the son who was to rule all the nations with an iron sceptre, and the child was taken straight up to God and to his throne,”

The Boy is Jesus, who is “to rule all the nations with an iron sceptre” according to the prophecy of Psalm 2 .

Psalm 2: 8-9 “8 Ask of me, and I shall give you the nations as your birthright, the whole wide world as your possession.

9 With an iron sceptre you will break them, shatter them like so many pots.’ )

The Boy’s Mother Is Mary

Rev: 12:17 “17 Then the dragon was enraged with the woman and went away to make war on the rest of her children, who obey God’s commandments and have in themselves the witness of Jesus.”

And in verse 17 Mary’s children are those “who obey God’s commandments and have in themselves the witness of Jesus”, that is all of us Christians.

Ps 132:8 “Go up, Yahweh, to your resting-place, you and the ark of your strength.”

The Ark of the Covenant had the power to bless and curse, and that it was the dwelling place of God's presence. (1 Samuel 4:3-7). The Ark of Covenant Can Destroy An Entire Planet & Everything on It (Revelation 11:19).

Our Mother St Mary is called “Tsion”. It means a mount, something that you would hide yourself in. When God told Lot to escape because he going to destroy Sodom and Gomorrah he told him “Escape for your life! Do not look behind you nor stay anywhere in the plain. Escape to the mountains, lest you be destroyed.” Genesis 19: 17. Our fathers symbolize St. Mary as the mountain that Lot hid in. King David also said “His foundation is in the holy mountains. The Lord loves the gates of Zion More than all the dwellings of Jacob.” Psalm 87:1. After stating that our Virgin Mary is the dwelling place of God and that she is also our refuge King David Continued to say “For the Lord has chosen Zion; He has desired it for His dwelling place: This is My resting place forever; Here I will dwell, for I have desired it” Psalm 132:13.

Just like The Ark of Covenant is where the commandments of God is written, God the Son dwelled in St. Mary. Kudus Efriem said in wdasie Mariam ZeArb (Friday) “ኮንኪ ታቦቶ ለፈጣሬ ሰማያት ወምድር” You have became the resting-place for the creator of the Heaven and earth.

Axum, a Holy City in Ethiopia’s northern Tigray region, whose main Church of Our Lady Mary of Zion is believed by Ethiopian Orthodox Christians to hold The Biblical Ark of The Covenant.

May the prayers of St. Mary be with us Amen

Sunday, November 30, 2025

A Massive Ethiopia-Map-Shaped Sunspot Nearly 50 times Larger Than Earth Has Appeared on The Sun

https://rumble.com/v72f4ei-a-massive-ethiopia-map-shaped-sunspot-nearly-50x-larger-than-earth-has-appe.html

https://www.bitchute.com/video/943FbpPd8IbX/

😇 ገብርኤል 🧕 ማርያም ❖ ኡራኤል ❖ ጊዮርጊስ ❖ ተክለ ሐይማኖት ❖ መርቆርዮስ ❖ ዮሴፍ ❖ መድኃኔ ዓለም

🌞 ከምድር ሃምሳ/50 እጥፍ የሚበልጥ ግዙፍ የሆነ እና የኢትዮጵያ ካርታ ቅርጽ ያለው የፀሐይ ጠብታ በፀሐይ ላይ ታየ

...እናም ጠብታው በየቀኑ እያደገ ነው.... ይህን ተዓምራዊ ክስተት ከአክሱም ጽዮን (ኅዳር ጽዮን)፣ በእሷ እና ጽዮናውያን ልጆቿ ላይ ከተከፈተው የዘር ማጥፋት ጂሃድ እና ከ 'ኤርታ አሌ(ሃይሊ ጉቢእሳተ ገሞ ፍንዳታ ጋር እናገናኘው። 

🧕 ቅድስት ማርያም የጽዮን ልጅ ናት = “ፀሐይን የተጐናጸፈች” ሴት = የቃል ኪዳኑ ታቦት

[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፩፲፱ ]❖

በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት በመቅደሱ ታየ፥ መብረቅና ድምፅም ነጐድጓድም የምድርም መናወጥ ታላቅም በረዶ ሆነ።“

❖[የዮሐንስ ራእይ ምዕራፍ ፲፪]❖

ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”

🧕 ማርያምና የቃል ኪዳኑ ታቦት በእግዚአብሔር መንፈስ “ተጸለሉ/ተሸፈኑ።”

[የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፩፴፭ ]❖

መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት። መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል።”

ጽዮንን ክበቧት” (መዝ.፵፯፥፲፪)

[መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፵፰]❖

እግዚአብሔር ትልቅ ነው፤ በአምላካችን ከተማ በተቀደሰ ተራራ ምስጋናው ብዙ ነው።

በሰሜን ወገን በመልካም ስፍራ የቆመ የምድር ሁሉ ደስታ የጽዮን ተራራ ነው፤ እርሱም የትልቁ ንጉሥ ከተማ ነው።

እግዚአብሔር በአዳራሾችዋ መጠጊያ ሆኖ ይታወቃል።

እነሆ፥ ነገሥታት ተከማችተው በአንድነት መጥተዋል።

እነርሱስ አይተው ተደነቁ፥ ደነገጡ፥ ታወኩ።

መንቀጥቀጥ እንደ ወላድ ምጥ በዚያ ያዛቸው።

በኃይለኛ ነፋስ የተርሴስን መርከቦች ትሰብራለህ።

እንደ ሰማን እንዲሁ አየን በሠራዊት ጌታ ከተማ፥ በአምላካችን ከተማ፤ እግዚአብሔር ለዘላለም ያጸናታል።

አምላክ ሆይ፥ በሕዝብህ መካከል ምሕረትህን ተቀበልን።

አምላክ ሆይ፥ እንደ ስምህ እንዲሁም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ምስጋናህ ነው፤ ቀኝህ ጽድቅን የተሞላች ናት።

፲፩ አቤቱ፥ ስለ ፍርድህ የጽዮን ተራራ ደስ ይበለው፥ የአይሁድም ሴት ልጆች ሐሤት ያድርጉ።

፲፪ ጽዮንን ክበቡአት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ፥ ግንቦችዋንም ቍጠሩ፤

፲፫ በብርታትዋ ልባችሁን አኑሩ፤ አዳራሽዋን አስቡ፤ ለሚመጣው ትውልድ ትነግሩ ዘንድ።

፲፬ ለዓለምና ለዘላለም ይህ አምላካችን ነው፥ እርሱም ለዘላለም ይመራናል።

መጽሐፈ ኦሪት ዘፀአት የታቦተ ጽዮንን ነገር እንዲህ ይተርከዋል። ሙሴ እስራኤልን ከካራን ወደ ከነዓን ይዞ ሲወጣ በሲና ተራራ ፵ መዓልትና ሌሊት ከዘረጋ ሳያጥፍ ከቆመበት ሳይቀመጥ በፍጹም ጽሙና ሁኖ በጾምና ጸሎት እግዚአብሔርን ጠየቀው። የለመኑትን የማይነሣ የጠየቁትን የማይረሳ እግዚአብሔርም ዐሥርቱ ትእዛዛት የተጻፈበትን ሁለት ጽላት ለሙሴ ሰጠው። ሙሴም ወደ ሕዝበ እስራኤል ይዞ ወረደ። እስራኤል አሮንን አስገድደው፤ በጌጦቻቸው የጥጃ ምስል ያለው ጣዖት ሠርተው እያመለኩ ቢጠብቁት ሙሴ ከእግዚአብሔር የተቀበለውን ታቦት ሰበረ። ዳግመኛም እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ቀድሞዎቹ አድረገህ ቅረጻቸው ብሎ ጽላትን እንዲያዘጋጅ አስተማረው። ሙሴም እንደታዘዘው አድርጎ ሠራ። (ዘፀ.፳፬ እና ፳፭) ‹‹ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ሙሴ ጽላቶቹን ባይሰብር ጽላትን መሥራት እንዴት ይቻል ነበር? (ሮሜ ፰፥፳፰)

ለ፭፻ ዓመታት ገደማ በእስራኤል ብዙ ገቢረ ተአምራትን ስታደርግ የነበረችዋ ይህች በሙሴ የተቀረጸች ታቦት በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል ለኢትዮጵያ ተሰጠች። (መጽሐፈ ክብረ ነገሥትን ሙሉውን ያንብቡ) የቤተ ክርስቲያን መረጃዎች ስለ አመጣጧ እንዲህ ያስነብበናል፤ ‹‹በማእከላዊ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት አክሱም ከተማ የምትገኘው ታቦተ ጽዮን በቀዳማዊ ምኒልክ ከኢየሩሳሌም መጥታ በምኩራብ ትኖር ነበር። ይህም ከጌታ ልደት በፊት ፱፻ ዓመት ገደማ ነው።›› (የቤተ ክርስቲያን መረጃዎች፣ በሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት፣ ገጽ ፪፻፭)

በምኩራብ ብትቆይም አብርሃ እና አጽብሐ የተባሉት ነገሥታት ፲፪ መቅደስ ፸፪ አዕማድ ያላት የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን አሠርተውላታል። ቀጣዩ ቤተ መቅደስ በዐፄ አንበሳ ውድም ተሠርቷል፤ ይህን ደግሞ ግራኝ አቃጠለው፤ መልሰውም ዐፄ ፋሲል አሠርተውታል፤ አሁን ያለውን ደግሞ በዘመናዊ መንገድ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ አሠርተዋል፤ ይህን ተከትሎም የጽዮን በዓል በታላቅ ድምቀት ኅዳር ፳፩ ይከበራል።

ኢትዮጵያ ሀገረ እግዚአብሔር ናት ከምትባልባቸው ምክንያቶች አንዱ ይህ የጽላተ ሙሴ ወደ ሀገራችን መምጣት ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ኅዳር ፳፩ ቀን በታላቅ ክብር ታከብረዋለች፡፡ በዚሁ ዕለት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወዳጆች ምእመናን በዓሉን ለማክበርና ለመሳለም ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን በብዛት ይገሠግሳሉ፡፡ ዕጣን፣ ጧፍ፣ ዘቢብና መባ ይሰጣሉ፡፡ ካህናቱም ከዋዜማው ጀምረው በከበሮና በጸናጽል ስብሐተ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፡፡ በድርሳነ ጽዮን መጽሐፍ እንደተገለጠው በጽዮን ፊት እንደ የመዓርጋቸው ቆመው ‹‹ዕግትዋ ለጽዮን ወህቀፍዋ፤ ጽዮንን ክበቧት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ›› የሚለውን መዝሙር ከዳዊት እያወጣጡ ይጸልያሉ፤ ይዘምራሉ፡፡ ፈጣሪያቸውን እያመሰገኑ የታቦተ ጽዮንን ተራዳኢነት በምእመናን ፊት ይመሰክራሉ፡፡ (መዝ. ፵፯፥፲፪)

ታቦት የአመቤታችን ምሳሌ ነውናም ነቢያት ስለ ክርስቶስ በተለያየ ኅብረት፣ ትንቢትና አምሳል እንደ ተናገሩ ሁሉ ክርስቶስ ስለሚገኝባት አማናዊት ድንግል ማርያምም ተናግረዋል፤ እግዚአብሔር ወልድ ወደዚህ ዓለም በሥጋ ማርያም ከመገለጡ በፊት ከእግዚአብሔር ተልከው ሕዝቡን ከአምልኮተ ጣዖትና ከገቢረ ኃጢአት እንዲጠበቅ የሚመክሩ፣ የሚያስተምሩና የሚያጽናኑ ነበሩ፡፡ (ሉቃ.፲፮፥፲፯፣ኢሳ.፵፥፩፣ኢሳ.፵፬፥፩-፲፩) የነቢያት ትንቢት ዋናው ዓላማም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቡን እንደተዋቸው እንደማይቀር፣ ወደዚህ ዓለም መጥቶ. ሰው ሆኖ ተገልጦ. ወንጌልን አስተምሮና ስለ እኛ መከራን ተቀብሎ እንደሚያድነን መግለጥ ነበር፡፡ በዚህም ስለ እግዚአብሔር ማደረያ እመቤታችን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ (ኢሳ.፯፥፬፣ማቴ.፩፥፳፫፣ሚክ. ፭፥፪)

በታቦት ሰሌዳ ላይ ‹አልፋ ወዖ› የሚለው ስመ እግዚአብሔር እንደተቀረጸ ሁሉ በአማናዊቷ ታቦት በእመቤታችን ማሕፀንም ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀርጿል። በዚህ ዕለት በኢትዮጵያ የሚከበረው ታቦተ ጽዮን ባለችባት አክሱም ብቻ አይደለም። በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በተለያዩ ቦታዎች ይከበራል።

ስለዚህም ተወዳጆች ሆይ! ጽዮንን እንክበባት! በእርሷ ምልጃና ጸሎት እንዲሁም ተራዳኢነት አምላካችን እግዚአብሔር ምሕረቱን ያወርድልን፣ ሰላምና ፍቅር ይሰጠን ዘንድ!

የአምላካችን የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም አምላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!

🧕 St. Mary is The Daughter of Zion = The Woman “Clothed with THE SUN” = The Ark of The Covenant

🧕 November 30, 2020 – Today, The Ethiopian Orthodox Tewahdo Church celebrates The Feast Day of The Ark of the Covenant | Hidar Tsion. It is one of the 33 Holidays that Our Church has put for St. Mary.

🌞 Something Wild is Happening on The Sun’s Hidden Side Right Now

For days, the far side has been vomiting one colossal coronal mass ejection after another, an almost unbroken firehose of billion-ton plasma clouds blasting into space at millions of kilometers per hour.

On Nov. 13, 2025, the doomed C/2025 K1 (ATLAS) comet exploded into pieces.

🌞 A Massive Hole Has Opened on The Sun

A massive Ethiopia-map shaped sunspot nearly has just appeared on the Sun and it’s growing every single day.

🌞 A massive Ethiopia map-shaped hole more than 50 times larger than Earth has opened on the sun, sending a powerful stream of solar wind our way. This breathtaking cosmic phenomenon is not just a feast for astronomers but a real-time event that could impact life here on Earth.

Captured by NASA’s Solar Dynamics Observatory between Monday and Thursday, the hole spans an astonishing 186,000 miles—enough space to line up over 23 Earths side by side. Known as a coronal hole, this dark region on the sun’s surface forms when magnetic fields open up, allowing charged particles to escape as high-speed solar wind.

Coronal holes are like gateways where the sun’s magnetic field stretches and lets wind rush out into space. The solar wind emerging from this particular butterfly-shaped hole is racing toward our planet and is expected to make landfall by Sunday.

This solar wind carries with it charged particles that can interact with Earth’s magnetic field. When this happens, we may experience geomagnetic storms—disturbances that can trigger both technological glitches and spectacular natural shows like the northern and southern lights.

What does this mean for Earth

According to Spaceweather.com, the solar wind from this vast coronal hole could bring geomagnetic storms classed between G1 and G2. This scale runs from G1 (weak) to G5 (extremely strong). Although these storms are relatively mild to moderate, they can still shake up satellites, disrupt communication networks, and even cause brief blackouts.

For anyone relying on GPS or airline communications, disruptions may become noticeable during such events. On the other hand, people living closer to the poles could witness stunning auroras—colorful waves of light caused when solar particles collide with molecules in Earth’s atmosphere.

Why equinoxes tend to increase geomagnetic storms

You might ask why these storms often peak near equinoxes, the times in March and September when day and night are almost equal. During these periods, the Earth’s axis aligns in a way that lets the sun’s magnetic field interact with our planet more intensely.

This phenomenon is linked to the “Russell-McPherron effect,” discovered in 1973, which predicts heightened geomagnetic activity around the equinoxes. Historically, data from 1932 to 2014 shows that such storms occur twice as often near equinoxes compared to solstices in June and December.

While these storms can interfere with electrical grids, satellites, and communication systems, they also reward us with some of the most mesmerizing natural light shows on Earth. The auroras, glowing in greens, reds, and purples, captivate all who see them. These celestial dances are nature’s way of showing us the powerful connection between the sun and Earth.

As this giant Ethiopia map-shaped hole pushes solar winds toward us, it’s a perfect moment to reflect on how deeply we are connected to the sun’s rhythms. Have you ever noticed changes in the sky or your devices during a solar event? Share your experiences and join the conversation on how space weather shapes our lives.

🧕 The Mother God, St. Mary, the New Ark of the Covenant

In the Book of Revelation (11:19) the Ark of the Covenant appears again, this time in the Celestial Temple in fulfillment of the prophecy of Jeremiah. This vision of The Ark leads immediately in revelation to the vision of the woman clothed with THE SUN who was with child (rev. 12:1). The image is that of Mary, presented as Mother of the Messiah and spiritual Mother of Israel, the New Ark of the Covenant.

Mary as the Ark of the New Covenant – Revelation

Rev: 11:19 “19 Then the sanctuary of God in heaven opened, and the ark of the covenant could be seen inside it. Then came flashes of lightning, peals of thunder and an earthquake and violent hail.”

Immediately following this verse we read of the “woman, robed with the sun, standing on the moon, and on her head a crown of TWELVE/ 12 stars”. The Ark of the Covenant as we have seen above, is none other than Mary, Jesus’ mother, so Mary is the woman spoken of here. (Remember that chapter numbers were only added to the bible in the twelth century, and verse numbers in the sixteenth century.)

Rev: 12:1 “1 Now a great sign appeared in heaven: a woman, robed with the sun, standing on the moon, and on her head a crown of twelve stars.

Rev 12: 4-5 “4 Its tail swept a third of the stars from the sky and hurled them to the ground, and the dragon stopped in front of the woman as she was at the point of giving birth, so that it could eat the child as soon as it was born.

5 The woman was delivered of a boy, the son who was to rule all the nations with an iron sceptre, and the child was taken straight up to God and to his throne,”

The Boy is Jesus, who is “to rule all the nations with an iron sceptre” according to the prophecy of Psalm 2 .

Psalm 2: 8-9 “8 Ask of me, and I shall give you the nations as your birthright, the whole wide world as your possession.

9 With an iron sceptre you will break them, shatter them like so many pots.’ )

The Boy’s Mother Is Mary

Rev: 12:17 “17 Then the dragon was enraged with the woman and went away to make war on the rest of her children, who obey God’s commandments and have in themselves the witness of Jesus.”

And in verse 17 Mary’s children are those “who obey God’s commandments and have in themselves the witness of Jesus”, that is all of us Christians.

Ps 132:8 “Go up, Yahweh, to your resting-place, you and the ark of your strength.”

The Ark of the Covenant had the power to bless and curse, and that it was the dwelling place of God's presence. (1 Samuel 4:3-7). The Ark of Covenant Can Destroy An Entire Planet & Everything on It (Revelation 11:19).

Our Mother St Mary is called “Tsion”. It means a mount, something that you would hide yourself in. When God told Lot to escape because he going to destroy Sodom and Gomorrah he told him “Escape for your life! Do not look behind you nor stay anywhere in the plain. Escape to the mountains, lest you be destroyed.” Genesis 19: 17. Our fathers symbolize St. Mary as the mountain that Lot hid in. King David also said “His foundation is in the holy mountains. The Lord loves the gates of Zion More than all the dwellings of Jacob.” Psalm 87:1. After stating that our Virgin Mary is the dwelling place of God and that she is also our refuge King David Continued to say “For the Lord has chosen Zion; He has desired it for His dwelling place: This is My resting place forever; Here I will dwell, for I have desired it” Psalm 132:13.

Just like The Ark of Covenant is where the commandments of God is written, God the Son dwelled in St. Mary. Kudus Efriem said in wdasie Mariam ZeArb (Friday) “ኮንኪ ታቦቶ ለፈጣሬ ሰማያት ወምድር” You have became the resting-place for the creator of the Heaven and earth.

Axum, a Holy City in Ethiopia’s northern Tigray region, whose main Church of Our Lady Mary of Zion is believed by Ethiopian Orthodox Christians to hold The Biblical Ark of The Covenant.

May the prayers of St. Mary be with us Amen

[Psalm 48]❖

Zion, the City of Our God

1 Great is the Lord and greatly to be praised in the city of our God! His holy mountain,

2 beautiful in elevation, is the joy of all the earth, Mount Zion, in the far north, the city of the great King.

3 Within her citadels God has made himself known as a fortress.

4 For behold, the kings assembled; they came on together.

5 As soon as they saw it, they were astounded; they were in panic; they took to flight.

6 Trembling took hold of them there, anguish as of a woman in labor.

7 By the east wind you shattered the ships of Tarshish.

8 As we have heard, so have we seen in the city of the Lord of hosts, in the city of our God, which God will establish forever. Selah

9 We have thought on your steadfast love, O God, in the midst of your temple.

10 As your name, O God, so your praise reaches to the ends of the earth. Your right hand is filled with righteousness.

11 Let Mount Zion be glad! Let the daughters of Judah rejoice because of your judgments!

12 Walk about Zion, go around her, number her towers,

13 consider well her ramparts, go through her citadels, that you may tell the next generation

14 that this is God, our God forever and ever. He will guide us forever.

🌈 Amazing Rainbow and Ethiopian Map Appear | አስደናቂ ው የማርያም መቀነት እና የኢትዮጵያ ካርታ መታየት

https://axumitethiopia.blogspot.com/2025/09/amazing-rainbow-and-ethiopian-map-appear.html

🌈 መስከረም ፭ (አቡዬ)፣ ፳፻፲፰ ዓ./ September 15, 2025

'የሔኖክ ሰማይ ሰሌዳ”(ልክ በኢትዮጵያ ሰማይ አቅጣጫ)


Dr. Fauci is A Liar: Tulsi Gabbard Releases Evidence Against Italo-American Fauci

https://www.bitchute.com/video/iX7lwMS8RhcX/ https://rumble.com/v7bjjvs-dr.-fauci-is-a-liar-tulsi-gabbard-releases-evidence-against-italo-am...